☞ ORION BANANA ማስቲካ ከ1996 ዓ/ም ጀምሮ (በግምት) ጥቂት ከሚባሉ ጊዜያት በቀር ከኪሴ ተለይቶኝ አያውቅም ነበር። ተመሳስሎ ሲሰራም ከአስመጪው ከአልሳም ትሬዲንግ ሁሉ ቀድሜ የማውቀው እኔ ነኝ ብል ማጋነን አይሆንም። ሃሃሃ… ስንቱን እንደከተብኩለት ቢያውቅ ኖሮ ተቆራጭ ያስብልኝ ነበር። (ተቆራጭ ኬክ ነው? ብሎ መቀለድ አይቻልም። ሄሄሄ…) ባለፈው የሀዘኑ ጊዜ ‘በየመንገዱ ማስቲካ ማኘክ አይቻልም።’ የሚል ተባራሪ ወሬ ሰምቼ የተውኩት፥ ይሄው እስከዛሬ አፌ ገብቶ አያውቅም።
Oh my Orion, I missed u so much!:D
☞ በ1993 ዓ/ም የ11ኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ በ1 ብር ከስሙኒ (1:25) የገዛሁትን ጥፍር መቁረጫ ነው እስከዛሬ ድረስ የምጠቀመው። ውይ ደጉ ዘመን… ብር ከስሙኒ የሚባል…እቃ የሚገዛ ብር ነበረን። ምናምን ብለን እናማር እንዴ? ሃሃሃ… የምር ግን በየመሀሉ ለአፍታ ከዐይኔ እየተሰወረች ሳጣት ሌላ ብገዛም ሳይቆይ ይሰበርብኛል። ያኔም ጥንካሬና አለመሰልቸቷን ውለታ እየቆጠርኩ እወለውላታለሁ። ምናልባት ለልጄ አወርሳት ይሆናል እያልኩ።…ሃሃሃ (ሰው ጠብመንጃ ሲወለውል፣ ቤት ሲያወርስ አይተሀል።’ ብሎ መቀለድ አይቻልም።) ተመስገን! እነሆ እኛም ድሮ ቀረ እያልን ያለበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡
Oh my nail cutter, I owed a lot to you! :p
☞ በ1997 ዓ/ም የ3ኛ ዓመት ተማሪ ሳለሁ በ35 ብር የገዛኋት አንዲት የምታምር ነጭ ቲሸርት አለችኝ። በጣም ስለምወዳት ብዙ ጊዜ እለብሳታለሁ። እርሷ ግን ለመጣል ፈቃደኛ አይደለችምና ዛሬም ያኔ በነበረችበት ይዞታ ላይ ሆና ታባብለኛለች። ሰሞኑን (ከ3 ወር ወዲህ) ባመጣሁት ክብደት የመጨመር ፕሮግራም መሰረት ያቀድኩትን ያህል በመጨመሬ ምክንያት እርሷም እንደሌሎቹ ልብሶቼ እየጠበበችኝ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው። እንዴት ነው እናጫርታት? ወይስ መልሰን ክብደት የመቀነስ ስራ (z other way round) እንጀምር?:) (ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ’ ብሎ መተረት ከቅናት ይቆጠራል። ሄሄሄ…)
Oh my t-shirt, I don’t wanna lose you!;)
☞ በ1992 ዓ/ም የአስረኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ጋሽ ዓለሙ የሚባሉ ባዮሎጂ መምህራችን (አዲስ ከተማ የተማሩ ያውቋቸዋል። ወይም ደግሞ በትርፍ ጊዜያቸው የመስመር ዳኝነት (አራጋቢነት) ስራ ስለሚሰሩ ምናልባት ስታዲየም የሚያዘወትሩ ወዳጆች ያውቋቸው ይሆናል።) በትምህርት መሀል ‘ጉንፋን ሊጀምር ሲል (ስሜቱ ሲመጣ) አፍንጫን በቀዝቃዛ ውሀ በመታጠብ ጉንፋኑን ሳይመጣ በፊት ድራሹን ማጥፋት ይቻላል፡፡ ያው ክትባት በሉት።’ ብለው ነገሩን። እነሆ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ እኔም ምክራቸውን ተግባር ላይ እያዋልኩ (ለሰውም እየመከርኩ) ጉንፋንን እከላከላለሁ።:) በመሆኑም ከዚያ ወዲህ ጉንፋን ይዞኝ የሚያውቀው በጣም ጥቂት ጊዜ ነው። እርሱም ክትባቴን ስረሳት! (‘ውሀ በመንደሩ ሲጠፋ ሲጠፋ…’ በል እንጂ ብሎ ማላገጥማ አይቻልም። ሃሃሃ…)
Oh common cold, where are you?:-/