አይደብርም?!

ከዚህ በፊት በተለያየ ጊዜ ብዙ የሀሰት ምስክርነቶችን ሰምተናል፡፡ እንደ ምሳሌ፡ ‘የተኩላው ለምድ ሲገፈፍ‘ የሚል ቪዲኦ ላይ መንገደኛ የኔ ቢጤን ‘አቡን ነበርኩ’ (አቡነ ያሬድ) አስብለው… ኋላ ላይ ‘ጌታን ተቀበለ’ ተብሎ ትልቅ ፌሽታ ሲደረግ የሚያሳይ ምስል ታይቶ….ቆይቶ ነገሩ ሲጣራ ግን ሰውየው የኔ ቢጤ እንደነበር እና ተክፍሎት እንደሆነ ታወቀ፡፡ በርሱም ብዙ አልን፣… አስባልን፣… ተባባልን….

እነሆ አሁን ደግሞ ኤርሚያስ የተባለ ሰው በቴዲ ድምፅ አስመስሎና የቴዲ እንደሆነ አድርጎ መዝሙር ለቅቆ…. ‘ቴዲ አፍሮ ፕሮቴስታንት ሆነ’ ተብሎ በሰፊው እየተወራ ነው፡፡ — ውስን ፕሮቴስታንቶችን እያስፈነጠዘ….ውስን ኦርቶዶክሶችን እያሳዘነ…. አሉባልተኞችን ደግሞ ወሬውን እያስቀባበለ…

ዘማሪው ያን ማስባል አለማስባሉን (እንዲባልለት መፈለግ አለመፈለጉን) …ወይም በርሱ እውቅና መደረጉን አላውቅም፡፡ ሆኖም ግን ቴዲን ለመምሰል በእጅጉ ደክሟልና፣ መመሳሰሉ ሆን ተብሎ አይደለም ለማለት ይከብዳል፡፡ እንዲያው ለጨዋታ ያደረገው ጎረምሳ ነው እንዳንል ደግሞ፣ ጥንቅቅ ተደርጎ በመሳሪያ የተቀናበረ ቆንጆ ድምፅ ነው የሚሰማው፡፡

ግን በውሸት ይህ በመሆኑ አትራፊው ማነው? የምሩን ጠፍቶ ሲሆን በአንድ በግ መገኘት (መመለስ) በሰማይ ትልቅ ደስታ እንደሚደረግ እናውቃለን (እናምናለን) …ግን በእነዚህ የሀይማኖት ሰዎች (ሀላፊዎች) ዘንድ በአንድ ሰው እምነቱን መቀላቀል ወሬ ስንት ብር ይሆን የሚገኘው? የቴዲ ፕሮቴስታንት መሆን ፕሮቴስታንቱን ያጠነክረዋልን? ኦርቶዶክሱንስ የላላዋልን? …ያም ይቅር፣ የእግዚአብሔርን መታመን ይወስነዋልን? በዚህስ ምን ያህል ሰው ለማትረፍ ታስቦ ይሆን?…

በእውነት እንዲህ ያለው ዘመቻ የሚደረገው በሀይማኖት አባቶችና አገልጋዮች እውቅና ከሆነ  በጣም ያሳዝናል፡፡ — በዛሬ ማዳን ሰበብ ከነበሩበት ጎዳና አስወጥተው መንገድ ላይ በአውላላው ስለሚጥሏቸው ነፍሳት አላሰቡምና፡፡ በዚያም ላይ በራሱ አፍቃሪ – ቴዲዎችም አሉና… ያም ሆነ ይህ ድርጊቱ ነውር በመሆኑ ሊወገዝ ይገባዋል፡፡

እጓለ ገብረ ዮሐንስ የተባሉ ሊቅ በ1956 ካሳተሙት “የከፍተኛ ትምህርት ዘይቤ” ከተሰኘ መፅሀፍ ላይ ይህቺን ጠቀሼ ላብቃ፡፡…

“ባሮጌ ቤት የሚኖረውን ሰው ተጥግቶ ቤትህ የማይረባ ነው ማለት አይገባም፡፡ ከበረቱ አጠገብ አዲስ ቤት መስራት ነው፡፡ ይህ አዲሱ ቤት ስለራሱም አዲስነት ሰለሌላውም አሮጌነት ይናገራል፡፡….እውነት የራስዎም የውሸትም ማስረጃ ናት”

ለግጥምጥም…!

ደርዘን በሞላ ቀን፣
ደርዘን በሞላ ወር፣ 1
በኮራ፣ በደራ፣ በ12..12..12.. ድርደራ፣

በፈረንጆች ስሌት. . . በፈረንጅ ቆጠራ፣
ሁለት ሺ ደፍኖ፣ ደርዘን ባ’ከለ አመት፣
የደርዘን ዙር ፍቅሬን… እነሆኝ ልዘክር፣
ላ’ባዛ፣ ላ’ካፍል፣ ልቀንስ፣ ልደምር፣
የፍቅርሽን ብዛት፣ የውድሽን ስፍር…
ቤት ውዬ ልቀምር…፤
ተረጂኝ ዓለሜ – እርጂኝ የ’ኔ ፍቅር… Silhouetted Woman Running at Sunset
ገስግሽ ወደ ቤቴ፣ ጓዝሽን ሸክፈሽ፣
ለቆጠራ ብቁ – አለ – ያልሽውን ይዘሽ፣
ትዝታሽን አዝለሽ፣ ተስፋሽን ሰንቀሽ፣
ድረሽ ከመደቤ፣ ተጠጊ ከልቤ፣
ዝለቂ ሰፈሬ፣ ግቢ ከመንደሬ፣
በእንዲ’ ያል የቀን ማማር፣
….በእንዲ’ ያለ ግጥምጥም፣
ካንቺ ይሁን ውሎዬ፣
….ካንቺ ይሁን አዳሬ፤እንዲያው ለግጥም ጥም
…ቃላት ሳበላልጥ፣ ቃላት ሳለካካ፣
ቃል ከቃል ሳጋጥም፣ አንጀት እንዲያረካ፣
እንዲሆን ለውሀ ጥም
– ምናልባት ከጠማን፣ ከቤት እንዳንወጣ፣
– ውሀ ምናባቱ!… ግጥም እንድንጠጣ፣
እንዲጥም፣ እንዲጥም…ልግጠምልሽ ደሞ…
እንዳልታየ ሰምሮ፣ እንዳልታየ ገጥሞ፣
ቃል ከቃል ተሳስሮ፣ እንደማያውቅ ቀድሞ፣
ቶሎ ነይ ዓለሜ!

እነሆ ቀለሙ፣… እነኋት ሀረጓ…
እነኋቸው ቃላት፣… እነሁልሽ አንጓ…
እነሁልሽ ብዕር… ሊገጥም ሲያዛጋ፣
ደግሞም…untitled
ወር ገብቶ በሰለስት፣ በሶስተኛ ቀኑ፣
በወር በአራተኛው…
ሁለት ሺህ አምስት… በሞላ ዘመኑ፣
– ‘ዘመነ ምህረት’…በሀበሾች ቆጠራ፣
ምህረት ይሁንልን፡፡

በሀበሾቹ ብቻ…
ሶስት እንትን ትዝታ፣
አራት እንትን ፍቅር፣
አምስት እንትን ተስፋ፣
ስድስት እንትን አንቺን… ደግም ከዚያ በላይ፣
የፍቅር አዱኛን፣… የመውደድን ሲሳይ፣
ሸክፈሽ ድረሺ…፤

በድርድር ሲቀመጥ፣ ቁጥር ተነባብሮ፣
ቀን ወር ተሰማምሮ፣ በዓመት ተጠፍሮ፣
እዪማ ዓለሜ…
…ሲያምር፡ – ለዐይን ለጆሮ…
3… 4… 5… እርሱ ራሱ ግጥም! — ሲጥም!
6ኛም አንቺ፣ – ‘የገጣሚው ንግስት፣
አጋጣሚ ዛሩ፣…ሂጂለት ከቤቱ፣
እየጠበቀሽ ነው፣ አጋጥሚው በሞቱ…’
…ይበሉሽ ሰዎቹ!
ተነሽ እመቤቴ፣
ብቅ በይ ከቤቴ፣
ምጪልኝ በሞቴ፡፡

ስራ የፈቱ ነጮች፣ ሚገጥሙለት ያጡ፣ እንደተነበዩት…
ምናልባት ከመጣ፣ በፈረንጆች ማርያም፣ በ21/12/2012፣
አንቺ ወዲያ ማዶ፣ እኔ ወዲህ ማዶ…
እንዳላስቀመጠን፣ አጉል ተበታትነን፣
እንዳያጣን ድንገት:-
— ከቤት ከቦታዬ፣ ከቦታሽ ከጎኔ…
ሲፈልግ አግኝቶን
— ካላሰበን ቦታ፣ እንዳይሆን ኩነኔ፣
በይ ነይ ላንቆላጵስሽ…

ቃል እየመራረጥኩ፣ ሌሊቱ እስኪነጋ፣ romance
የግጥምጥሞሹን፣ – ልግጠምልሽ በቃ፣
እስኪደርስ ቀኑ፣ አምላክ እስኪመጣ፣
እንበል ‘ማራናታ’፣
ባልነው ስራ የለም…
…እነሁልሽ ሰንበት፣ እነኋት በዓታ፣
– የታህሳስ በዓታ፣ ነጋሿ – የአመቷ…

ለውድሽ በረከት፣ ለፍቅርሽ ስጦታ፣
ስንኙን ላሰናኝ፣ ቤት ከቤት ላማታ፣
ወርቁን ሰም ልቀባ፣ ቅኔ ልሰር ልፍታ፣
አበርቺኝ ልበርታ፣ ይሁንልን ፌሽታ!
ዓለሙን ይግረመው፣ አንቺንም ይግረምሽ፤
እኔንም ይግረመኝ…፤
በይ ነይ ልግጠምልሽ! ልበልሸ ባይገርምሽ፤
ባይገርምሽ….ባይገርምሽ….ባይገርምሽ….

/ዮሐንስ ሞላ/
12/12/12
03/04/05 Only  Ethiopian