መላ ብሎ ዝም!

አሁን ጠይም በረንዳ: ዘ ዮሐንስ ሞላ/ Chocolate Porch: Yohanes Molla’s ላይ መለስ ቀለስ በማለት ውሀ ልኩን፣ ስፋት ጥበቱን ቃኝተን ስናበቃ፣ ጨረቃን እያደነቅን ያለበት ሁኔታ ነው ያለው። የምር ግን ጨረቃዋን ጠቅልሎ ይዞ ቤት መግባት ቢቻል እንዴት አሪፍ ነበር?! ኡኡቴ… ሲሉ ሰምተን! ሄሄሄ….
ዛሬ በወፍ በረር ኢቲቢ3 ላይ “መላ” የተሰኘ ፕሮግራም ተመልክተን ነበር። ‘በወፍ በረር’ ማለታችን ለወሬያችን ጥራት እርግጠኛ መሆን ስለማንችል ነው። እኔ ወሬው ጆሮዬ ሲገባ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እየተወያዩ ነበር። የውይይቱ ርዕስ – “ፍቅር ያስፈልጋል አያስፈልግም?” የሚል ነበር።
እንግዲህ በሰላም ለመኖር፣ ትውልድ ለማስቀጠል መሰረታዊ ስለሆነው ፍቅር መላ ሊመታ ነው ውይይቱ የታለመው።…የተፈጠርንበትን ዓላማ (በተለይ ማንም ከወሰን በላይ ምድር ላይ ሊኖር ካለመቻሉ ጋር አነፃፅረነው) ስተው በማያፋጨው ሀሳብ አፋጩ። ከዚያም የአንድ ጉብል አስተያየት ባለፈው ስለቃላት ውርርስ ከፈተልነው ጋር ገጥሞ ጆሮዬን ያዘው፤ እንዲህ አለ…”በሰው ልጆች ህይወት ውስጥ ፍቅር የአንበሳውን ድርሻ ይይዛል!”…እኔም በሆዴ “አንበሳ ይብላህ!”!! ሃሃሃ…

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s