“ሀብት አልቦ መናጢ፣ የነጣ የገረጣ፣
እንኳን የሚያበላኝ፣ የሚበላው ያጣ፣
… ነው!!”
ብለሽ አትሽሺኝ፣
አደራሽን ውዴ!!
ችጋር እስኪጠፋ፥ ከላዩ ተቀርፎ
የደሀ አዳሩ – ባይሞላ ችሎ አልፎ
በፍቅር ተቃቅፎ፣ ገላው ተቆላልፎ
ባይበላ ታርሶ፣
… አፍ ላፍ ተጎራርሶ፤
… ምራቅ ተደባብሶ፤
… ምላስ ተላልሶ፤
ነውና!
/ዮሐንስ ሞላ – 1995 ዓ/ም/
“ሀብት አልቦ መናጢ፣ የነጣ የገረጣ፣
እንኳን የሚያበላኝ፣ የሚበላው ያጣ፣
… ነው!!”
ብለሽ አትሽሺኝ፣
አደራሽን ውዴ!!
ችጋር እስኪጠፋ፥ ከላዩ ተቀርፎ
የደሀ አዳሩ – ባይሞላ ችሎ አልፎ
በፍቅር ተቃቅፎ፣ ገላው ተቆላልፎ
ባይበላ ታርሶ፣
… አፍ ላፍ ተጎራርሶ፤
… ምራቅ ተደባብሶ፤
… ምላስ ተላልሶ፤
ነውና!
/ዮሐንስ ሞላ – 1995 ዓ/ም/