ዛምቢያ -ሉሳካ

መሳፍንት ባዘዘው
ብዙ ኢትዮያውያን ወገኖቻችን ሁለት አስርታት አመቶች ውስጥ፣ ሰርተው የመለወጥን ተስፋ ሰንቀው፣ ወደ ማንዴላዋ ደቡብ አፍሪካ ተመዋል። አሁንም ቢሆን መትመሙ ቀጥሏል። መቼ እንደሚያቆም አንድዬ ብቻ ነው የሚያውቀው። ከኢትዮጵያ ኬንያ ታንዛኒያ ሞዛንቢክ ደቡብ አፍሪካ አንዱ መንገድ ነው። ይህ መስመር ብዙዎቹን ወስዷል። ከሆነ ግዜ በኋላ ግን ታንዛኒያን ማለፍ እየከበደ መጣ። ስደተኞች እንደሚሉት ደቡብ አፍሪካ ታንዛንያን “እባክሽ ኢትዬጵያዊያንን እዛው መልሽልኝ! ውለታሽን አረሳም! ” ስላለቻት ነው።

ለዚህም ይመስላል የኔሬሬዋ ታንዛንያ አታልፏትም! አለች። ፖሊስ ከህዝቡ ጋር ተባበረ፣ ኢትዬጵያዊ ካያችሁ ጠቁሙ ጉርሻ አለው። እየተባለ በኪሲዋሊ ቋንቋ በየሚዲያው ተለፈፈ። “በውኑ ነብር ዥንጉርጉርነቱን ኢትዮጵያዊ መልኩን ሊለውጥ ይችላልን? ” እንዲል ቃሉ፣ ወገኔ ታንዛኒያ ላይ “እሩቅ አሳቢ ቅርብ አዳሪ ” ሆነ። ታንዛንያ እየያዘች ዲፖርት ብታደርግ መልካም፣ ህገ ወጥ ስደተኞችን የመቅጫ ህግ ስላላት፣ ወደ አሰቃቂ እስር ቤቶቿ ትወረውራቸው ጀመር ።

አሻጋሪዎች ሌላ መንገድ ቀየሱ ። ከናይሮቢ – ካምፓላ – ኪጋሊ – ቡጅንቡራ በባስ እያቆራረጡ ከተጓዙ በኋላ ከቡጁምቡራ እስከ ዛምቢያ ጠረፍ ድረስ ረዥሙን የታንጋኒካ ሃይቅ በጭነት መርከብ የቋርጡታል። ከዚያ በመኪና ወደ ዛምቢያ ዋና ከተማ ሉሳካ፣ ከሉሳካ እስከ ሞዛንቢክ ደቡባዊ ጫፍ በተቆራረጠ የመኪና ጉዞ፣ እዛ ከደረስክ በኋላ ትንሽ የእግር ጉዞ በአሻጋሪህ ፈትአውራሪነት በጨለማ ታደርግና የሽቦ አጥሮች ተቀደውለህ ሹልክ እያልክ ብለህ ወርቅ የምታፈሰውን፣ የማሪያ ሚከቢያን ደቡብ አፍሪካን ርግጥ!!

አነሳሴ ዛምቢያ ሉሳካ ላይ ፣ በአንድ ወቅት ሁለት ወር ከ 15 ቃናት ታስሮ የነበር ጓደኛዬ ያጫወተኝን መጥፎ ትዝታውን ላክፍልህ ነው። ፁሁፌ ዘልዛላ ቢጤ ቢሆንብህም ፣ ታገሰኝ!
ሉሳካ ፣ ትንሽ ናት። ትልቁን ጎዳናዋን “የሃይለስላሴ ጎዳና” ብላ ሰይማለች ። የተወሰወሰችብን ትመስላለች ፣ አዲስ አበባ ተብሎ የሚጠራም መንገድ አላት። ጓደኛዬ ቪዛው ባለቀ ፓስፖርት ሲዘዋወር ተያዘና ወደ እስር ቤት ተወረወረ።

እስር ቤታቸው፣ አራት ሜ በአራት ሜ ስፋት ባላቸው ትንንሽ ክፍሎች የተከፋፈሉ ናቸው። እያንዳንዳቸው ከመቶ በላይ የአዳም ዘርን አጭቀው ይዘዋል ። ለአየር ማስገቢያ አይቅርብን በማለት ይመስላል የአንዲት ጡብ ስፋት ታህል ቀዳዳ አለቻት ። ወደ ትንሿ ሲኦል ከመግባትህ በፊት አለባበስህ ቁምጣ ሱሪ ብቻ መሆን አለበት ። ቁምጣ ከሌለህ ሱሪህን ትቆምጣለህ ።

‘ሲሚንቶ ወለል ላይ ያለመንጣፍ እንዴት እጋደማለሁ?’ ብለህ እንዳታስብና ጓደኛዬ እንዳይስቅብህ!…መጋደም ብሎ ነገር የለም ። ቁጭ ብለህ ነው ምትተኛው። እግሮችህን ከፈት አድርገህ ቁጭ ትላለህ፣ በአንተ እግሮች ክፍተት ሌላው ቁጭ ይላል፣ በተመሳሳይ መስመር ሌላውም እንዲሁ ይደረደራል። አስበው… ደረትህ እና ጀርባው ፣ ሙርጡና እንትንህ ግጥም ይላሉ። በድቀድቅ ጨለማ ውስጥ እንዲህ ሁነህ “ትተኛለህ”…ፎርሙን ካዛነፍክ ቅጣት አለው።

ቤቷ ጄኔራል አላት። ጄኔራሉ ከመቶ መናምኑ እስረኛ ውስጥ ጉልበተኛው ነው። አቅሙ ካለህ ጄኔራሉን ገጥመህ አፈር ድሜ አብላው እና ንገስ! ጄኔራሉ 6 ፍራሾችን ደርድሮ ጧ ብሎ ይተኛል። የእርሱ ምክትል ቁጥር 1 ይባላል ፣ እርሱ ደግሞ 4 ፍራሾችን ደርድሮ የሚተኛ። ቁጥር 2 ሶስት፣ ቁጥር 3 ሁለት፣ ቁጥር 4 አንድ ፍራሽ ላይ ይተኛሉ። 3 ፖሊሶች አሉ ከሶስቱ አንዱ አለቃቸው፣ ብርድ ልብስ አንጥፎ ሲተኛ ፣ ቀሪዎቹ ሁለቱ ባዶ ወለል ላይ የብርድ ልብስ ቁራጭ ተንተርሰው ይተኛሉ።

የመጨረሻው የሥልጣን እርከን የፅዳት ሰራተኞች ናቸው። አራት ሲሆኑ ሰራቸው ጄኔራሉን መንከባከብ ነው ። ልብሱን ያጥባሉ፣ ዙፋኑን ያፀዳዳሉ… በአንድ ጎናቸው እግር እና እራስ እየሆኑ እንዲተኙ ተፈቅዶላቸዋል ። ምግብ በቀን አንዴ የተቀቀለ ቦሎቄ ከገንፎ ጋር ይሰጡሃል ። ከኋላህ ባለው የሰልፍ ግፊ ባላንስህን ስተህ ከጨላፊው ያጨላለፍ ምት ውጭ ሆነህ ምግብህ ቢደፋ አለቀልህ! ነገ በዚህ ስአት ተመሳሳይ ችግር እንዳይገጥምህ አምላክን ለምን… ለዛሬው ምራቅህን ዋጥ!

የካሉሻ ቧልያዋ ዛምቢያ እንዲህ ነች!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s