ሰርግና ምላሽ

‘ቀልቀሎ – ስልቻ፣ ስልቻ – ቀልቀሎ’ ይሉት ነገር ደርሶ፣
‘ተደጋገፉ’ አሉ፣ ጎን ለጎን ቆሙ፤ — ክብረት ተደርምሶ፤
ኩራት ተሽቀንጥሮ፣… ሰውነት ተንቆ፣… እርም ተበጣጥሶ፤
ለልብ ቅብብል፣ ለሀሳብ ፍጥምጥም፣ – ውል ፊርማ ታድሶ፣
ወኔ ተጠርምሶ፣… ብር – አጥር ፈራርሶ፣… ህግ ተገርስሶ፤

— የእኒ’ያ ባላንጣዎች!

ይሁና!!

/ዮሐንስ ሞላ/