‘ቀልቀሎ – ስልቻ፣ ስልቻ – ቀልቀሎ’ ይሉት ነገር ደርሶ፣
‘ተደጋገፉ’ አሉ፣ ጎን ለጎን ቆሙ፤ — ክብረት ተደርምሶ፤
ኩራት ተሽቀንጥሮ፣… ሰውነት ተንቆ፣… እርም ተበጣጥሶ፤
ለልብ ቅብብል፣ ለሀሳብ ፍጥምጥም፣ – ውል ፊርማ ታድሶ፣
ወኔ ተጠርምሶ፣… ብር – አጥር ፈራርሶ፣… ህግ ተገርስሶ፤
— የእኒ’ያ ባላንጣዎች!
ይሁና!!
/ዮሐንስ ሞላ/
‘ቀልቀሎ – ስልቻ፣ ስልቻ – ቀልቀሎ’ ይሉት ነገር ደርሶ፣
‘ተደጋገፉ’ አሉ፣ ጎን ለጎን ቆሙ፤ — ክብረት ተደርምሶ፤
ኩራት ተሽቀንጥሮ፣… ሰውነት ተንቆ፣… እርም ተበጣጥሶ፤
ለልብ ቅብብል፣ ለሀሳብ ፍጥምጥም፣ – ውል ፊርማ ታድሶ፣
ወኔ ተጠርምሶ፣… ብር – አጥር ፈራርሶ፣… ህግ ተገርስሶ፤
— የእኒ’ያ ባላንጣዎች!
ይሁና!!
/ዮሐንስ ሞላ/