የብርሃን ልክፍት በቅርብ ቀን…

540095_359925470795159_1890655638_n

ለተሰጠው ሰው፥ የእርግዝናን ጊዜ በሰላም አልፎ ልጅ መውለድ ቀላል ነው። ማሳደግና፥ (በውጭም በውስጥም) አሳምሮ ከማህበረሰብ መደባለቁ ግን የበለጠ ያደክማል።….. በዚሁ መስመር ሄጄ፥ እንደራሴ ልምድና መረዳት ሳስበውም፥ የፃፉትን አሳምሮ፣ ደረጃውን እንዲጠብቅ ተጨንቆና ስለአርትኦቱ፥ በዘርፉ ካሉ 522056_359599874161052_1690501995_nባለሞያዎች ጋር ተማክሮ፥ ለንባብ ማሰናዳቱ…. በተለይ ከመጻፍ ጋር ሲነፃፀር የበለጠ ያደክማል።
እውነት ነው! ፅሁፎቹን ስፅፍ ከነበረኝ ይልቅ… መመጠን አለመመጠናቸውን ለመረዳት ስመረምር፣ ከወዳጆች ጋር ስማከርና፣ በመጽሐፍ እንዲሆኑ ሳዘጋጅ ብዙ ደክሜያለሁ፤…. ስፅፋቸው ከፈጀሁት ጊዜ በላይ፥ ስለ መጽሐፍሳስብና ለመጽሐፍ ሳሰናዳቸው ፈጅቼያለሁ። “ምነው ማሳተም ባልኖረ!” ያልኩበት ጊዜማ ብዛቱ!አሳትሞ ማጋራቱን ሽሽት “ኧረ ምነው መፃፍ ባልወደድኩ ኖሮ!” አለማለቴም አንድ ነገር ነው።…ቢሆንም ግን፥ ዘርፉንና አንባቢን ከማክበር የመጣ ነውና ሲጀመር እንዳልነበረው ሲታለፍ ደስ ይላል፡፡

የሆነው ሆኖ ግን…. በወዳጆች ግፊትና፣ ሥራዎቼ ‘ለዘርፉ አስተዋፅኦ ቢያደርጉ’ በሚል የራስ ፍላጎት፣ የተነሳ ይህን መፃፍ ለማዘጋጀት ከወሰንኩኝ (ከራሴ ጋር ከተስማማሁ) ከአንድ ዓመት በላይ ሆኖኝ ነበር።… ከዚያም፥ አንዱን ሳነሳ ስጥል፣ አንዱን ስሰርዝ ስደልዝ፣ ‘እንዲህ ይሁን እንዲያ’ ስል ዛሬ ላይ ደርሼ “በቅርብ ቀን” በማለት የሽፋን ምስሉን (cover) ቀብድ ለማስያዝ በቅቻለሁ።:-) በእውነት ትልቅ እፎይታ ነው። የበለጠው እፎይታ ደግሞ መጽሃፉ ሲመረቅ ልንገናኝ ከፊት እንደሚቆየኝ ይሰማኛል፡፡

እውነቱን ለመናገር፥ መጽሐፉን ለማሳተም ወስኜ ዝግጅቱን ስጀምረው…. 305819_636911149659711_790201671_n“ከእኔ ይውጣልኝና ልገላገል”፣ “ወዳጆቼን ላስደስትና ጥያቄያቸውን በትህትና ልመልስ” “መጽሐፍ ቢኖረኝስ?”… ምናምን ከሚል ተራ ስሜትና ሞቅታ ሳይሆን፣ ለስነጽሁፍ ዘርፍ ሊሰጠው የሚገባውን ክብርና ፍቅር ለመረዳት በመጣር ነበር። በዚያም መሰረት “ይመጥናሉ” ያልኳቸውን ሰብስቤ “ይሆናል” ባልኩት አቀራረብ “የብርሃን ልክፍት”ን አዘጋጅቻለሁ። በዚህ ላይ የሚኖሩትን አስተያየቶች በመጠቀምና፣ በንባብ በመታገዝ ወደፊት (እድሜ ከሰጠን) የተሻልኩ እንደምሆን ግን አውቃለሁ፡፡

…. ከህብረተሰብ ጋር ከማቀራረብ ባለፈ፥ ለብዙ የታፈኑ ድምጾች ልሳን በመሆን ያገለግላልና ኢነተርኔት መጠቀም ደስ ይላል። ብዙ ጊዜ ይፍጅ እንጂ፥ ፌስቡክን ቀርቦ አውቆ፥ ኗሪዎቹን ማስተዋልና እርስበርስ ተቀራርቦ በነፃ መማማር ደግሞ ይበልጥ ደስ ይላል። — ያው ከነድክመትና ጉዳቱ ጋር ማለት ነው። በጊዜ እየተሻሻሉና በአጠቃቀም ረገድ እየጎለመሱ ሲመጡ ደግሞ፥ ድካሙም ጉዳቱም አብሮ ይቀንሳል።

በጽሁፍና በመጽሐፍ ዝግጅት መንገዴ ላይ፣ በአንድም በሌላም መልኩ አስተዋፅኦ አድርጋችኋልና፣ በክፋታችሁም በደግነታችሁም አብራችሁኝ (ዙሪያዬ) ለነበራችሁ በሙሉ ምስጋናዬ ከልብ ነው። እንኳን አወቅኋችሁ! ….እንግዲህ “ይሁን” ስትሉ የ”በቀርብ ቀን“ ወሬውን በዙሪያችሁ ሁሉ አዳርሱት።

Spread the news…. Share!!