ነበር…. ነበር…. ነበር….!?

ዛሬ፥ በልጅነታችን ለመልካም ምኞት መግለጫ የምንስላቸው አበባዎች፥ ስዕሎች፥ ፎርሞች፥ ትዝ አሉኝ።1184826_10200724059160132_498112269_n ከቡሄ በኋላ የምንጠመደው ፎርሞችን በመንደፍ፣ በማባዛትና ቀለም በመቀባት ነበር። በተለያዩ  ዲዛይኖች በA4 ወረቀቶች ላይ ስለን እናዘጋጃለን… ስዕል ላይ ጎበዝ ያልሆነ ደግሞ ጎበዝ ለሆኑት እየተላላከ ያስላቸዋል። ወይ ደግሞ የተሳሉትን በሳንቲም ገዝቶ ያዘጋጃል።
ጳጉሜን 5 ቀን የፎርም ቆጠራ እና የገቢ ቅድመ ስሌት ቀን ነበር። ከሰሞኑ በቀለም የተጨማለቀው እጅም በዚህ ቀን ተፈቅፍቆም ቢሆን ይጠራ ነበር። ከዚያ ሲነጋ፥ በየጎረቤትና ዘመድ ቤት “እንኳን አደረሳችሁ” እየተባለ አበባ ይሰጣል። ቀኑ ረፍዶ አበባ ያልወሰድኩባቸው (ረስ…ቼ) ቤት ሰዎች ይቆጡኝ እንደነበር ትዝ ይለኛል። …ቤትም፥ “ኧከሌ ቤት ውሰድ” እያሉ ች የረሳሁትን ያስታውሱኝ ነበር። ሴቶቹም አዲስ የተገዛላቸውን ልብስ በዋዜማው ለብሰው “አበባዮሽ” እያሉ በየቤተዘመዱና ጎረቤቱ ቤት እየዞሩ ይጨፍሩ ነበር።

ነበር…. ነበር…. ነበር….!?

በርግጥ አበባዮሽ የሚጨፍሩ ጥቂት ልጆች ዛሬም ይታያሉ። ለዛና አጨፋፈሩ ግን እየተበላሸ እየተበላሸ፣ ስሜቱም እየቀዘቀዘ፣ እየቀዘቀዘ ነው የመጣው። ሰዉም ለልጆቹ የሚሰጠው ምላሽ፥ ነገሩን ከልመና ጋር እያቀራረበው የሚያሳፍራቸውም ይመስለኛል። ….አበባ የሚስል ልጅ ግን፥ እንጃ! እስኪ ሲነጋ ይመጣልን አበባ ይኖር እንደው እንጠብቃለን።

….ወላጆችም ልጆቻቸውን እንዲህ ባሉ የበዓል እንቅስቃሴዎች ላይ እንዲሰማሩ የሚፈቅዱ አይመስለኝም። ከማጣትና ከመሳጣት ጋር ሲያገናኙት ይስተዋላል። ሆኖም ግን፥ በዓልና ባህል ከማግኘትና ከማጣት ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም። እናም፥ ከማሸማቀቅና ከመከልከል ይልቅ ሊያበረታቷቸው ይገባል። አበባ ሲስሉ ቀለም እናቀብላቸው…. አበባዮሽ ሲሉ ትክክለኛውን ዜማ እናስተላልፍላቸው….

“ሰዶ ማሳደድ ካማረህ፥ ዶሮህን በቆቅ ለውጥ” ይባላል፥… እናም፥ ኋላ ማሳደዱ እንዳያደክመን፥ እየጠፉ ያሉ ባህሎቻችንን እንንከባከብ። ስለመዝለቃቸው እንምከር።
 እንቁጣጣሽ!

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s