ንፉግ…!

ብር አምባሯን ሽቶ፣ ደፍሮ ለተጠጋ፣1471767_472678226186549_957489850_n
ሲግጣት ለኖረ፥ ለጅበ – ሰብ መንጋ፣
– ፍስሀ ስትታትር፣ ተድላ ስትተጋ፣
አዱኛ ስታጭቅ፣ ሲሳይ ስትሞላ፣
ዓለም ስታሳምር፣ ስታደልብ ገላ፤

ስጋዋን ቸርችራ፣ መታትራ፥ – ገብራ፣
ላቧን አንጠፍጥፋ፣ ደሟን አንቆርቁራ፣
ቆዳዋን ገሽልጣ፣ አጥንቷን ሰንጥራ፣
ተግጣ… ተግጣ… አልቃ፣ ተፈርፍራ፥
አዳርሳ ስትጨርስ…

ለታማኝ ጠባቂው፣ ለምስኪን ወገኔ፣67086_164321147058957_380093110_n
– ለሰነቀው ፍቅር፣ ለሸከፈው ወኔ፥
አንዠቱ ሲላወስ፣ ሆዱን መሸበቢያ፣
ለከርታታ ነፍሱ፣ ለዐይኖቹ ማረፊያ፣
ለስሜቱ ማ’ተም፣ ለልቡ መንቧቻ፣
ለውዱ ስልቻ፣ ለፍቅሩ ማንገቻ፣
ታንበሸብሻለች፥…
አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ቀለሟን ብቻ፤

/ዮሐንስ ሞላ/

 

 

ተረት ተረት…

በባዶ ቤት፥…ካደመቀው እሳት ብቻ፥
(ለዚያውም ጢስ የበዛበት፥
ሚንጨላጨል በ’ርጥብ እንጨት)
ከእሳቱ ዙሪያ — ጉልቻ…
ጉልቻው ጎን፥ — መወዘቻ፥
(ለወጉ የተሰተረ፥
ክክ የለሽ፥ ግብር አልባ
ሌጣውን የተገተረ…)

እኔና እናት ዓለሜ፥ ተቀምጠን ወለሉ ላይ፥
እሷ – ዓይን ዓይኔን፤… እኔ – እሳት ሳይ፥
ከላይ፥… ጣሪያዋ ደክማ፣
መውደቅ ይሻላት፥ ዘምማ፥
(ስታሾፍብን ነገር…)
ካጠገባችን ወስከምቢያ፥… እላዩ ላይ አሹቁ፥
የባቄላው፥… – ኀይል አድቅቁ፥
ጥርስ የሚይዝ፥… የሚያስጠማው…
ውኀ አንሶት፣ ጨው የበዛው፤
ስጡኝ ስጡኝ የሚያሰኘው…
በበረሀ፥…
በሌለበት ጭላጭ ውኀ፥ ‘ውኀ፣ ውኀ…’
ጠኔ አብርዱ፣ ፈስ አድምቁ…
አጫዋቹ፥ ዜማ አርቅቁ፥
ዝም አደፍርሱ፥ ድብርት አርቁ፥
ብሶት አጅቡ፣ ቁዘማ አሙቁ፤…
አሹቁ…

ቁርጥም ቁርጥምጥም ሳደርገው፥
እንዳያልቅብኝ ሳስቼ፣ ስጫወትበት ስከካው፤
እማንም ሲቆረጥማት፥…
በጉበኑ ሽንቁር ሾልኮ፥ ሲጫወትባት ቁርጥማት፥
እኔ እንድበላ ብላ፥
ቁርጠማውን እንደጠላ፥
እንደ ጠገበች መስላ…
ተኮራምታ፥….
እናት ዓለሜ ዘንካታ…
ቁጭ ብላ ከነኩራቷ፣
ከነታጠፈ አንጀቷ፥…
ተረት ትነግረኛለች…

እዛው በእዛው አሰማምራ፥
ከእኔ ስለ እኔ ፈጣጥራ፥
ጨዋታ ወጉን ጨማምራ፥
ምክር ተግሳፁን ቆጣጥራ፥
ፍቅር መውደዷን ሞጃጅራ፥…
“ተረት ተረት” ትለኛለች፥…
መሰረት በሌለው ቤት ውስጥ፥ “የመሰረት” እላታለሁ፥
ላም፣ በረት በሌለው ቤት ውስጥ “የላም በረት” እላታለሁ፤
ተረቷን ትቀጥላለች፥…
“እናትና ልጅ ነበሩ…”
– “እሺ”
“በአንዲት ደሳሳ ጎጆ ፥ በነጻ ፍቅር ሲኖሩ…”
– “እሺ”
“ሲኖሩ ሲኖሩ…”
– “እሺ”
“ከእለታት ባንድ ቀን…”
– “እሺ”
.
.
.
በመከራ አንድ ቀን፣ በችጋር አንድ ቀን፥
በአፈና አንድ ቀን፣ በበደል አንድ ቀን፥
በስደት አንድ ቀን፣ በድብደባ አንድ ቀን
በእስር አንድ ቀን፣ በውሸት አንድ ቀን…
ከእለታት ባንድ ቀን…
የባሎቿን ክፋት፥ የልጆቿን ልፋት፥
የተገላባጩን፣ አጎብዳጁን ብዛት፥
የውስጥ እግር ላሹን፥ ያሸርጋዱን ብዛት፥…
ያንንም… ያንንም… ታጫውተኛለች፤
የገዛ ታሪኳን በተረት መስላ፥
የገዛ ታሪኬን፥ ‘ተረት ተረት’ ብላ፤

ደግሞም ከስር ከስሩ፥ ‘ይሻል ቀን ይመጣል’፥
ብላ እያፅናናችኝ፥…
እምነት አስሰንቃ፣ ተስፋ እያስያዘችኝ፥
ታጫውተኛለች፥
እኔም “እሺ” እላለሁ…
“እሺ” ልበል እንጂ፥ ሌላ ምን አውቃለሁ?
ባውቅስ ምን እላለሁ?…ብልስ ማን ሊሰማኝ?
ከአምባው የገነኑት፥ አቆርቋዥ ገዦቿ፥
አቃቤ ሰቀቀን፣ ስግብግብ ሻጮቿ፥
ሆደ ዝርጣጦቹ፥ ሽግናም ባሎቿ፥
ተስፋዬን ሊቀሙ፥…. ሳቄን ሊያጨልሙ፥
ጉልበቴን ሊያደክሙ፥ ይንጠራወዛሉ…
ልጅነቴን ዳምጠው፥ ጉጉቴን ሊቀሙ፥ ይተራመሳሉ…
እናስ ምን እላለሁ?
– “እሺ” ልበል እንጂ እስከጊዜው ድረስ፥
.
.
ተረቷን ቀጥላ፥
ስደካክም ጊዜ የጨረሰች መስላ፥
“ተረቴን መልሱ
አፌን በዳቦ አብሱ።” ብላ ታፌዛለች…
ታሳቅቀኛለች…
ዳቦ እየቸገራት ለቅምሻ ለዝክር
አሹቅ እያገባች፥ ለራት ምሳ ግብር፥
“ዳቦ” ትለኛለች፥
– እንቆቅልሽ እማ፥
– ቅኔ እናት ዓለም
.
.
ይኸው ነው ወጋችን…
.
.
ስንኖር፥ ስንኖር፣
ስንኖር፥ ስንኖር…

ከእለታት ባንድ ቀን፥
ወጉ ደርሶኝ ዛሬ፥
አወራላት ጀመር፥ ተረት ቀማምሬ፥
ከራሷ መዝዤ፣ ለርሷው ቆጣጥሬ፥
ለራሷ ሰፍሬ፥ ከራሷ ቆንጥሬ፥
ወንድም እህቶቼን ልጆቿን ናፍቄ፥
በባሎቿ አፍሬ፥…
እንዲህ ጀመርኩላት….

“ተረት ተረት…”
– “የላም በረት”
“እንዴ… የላም በረት? …የቱን ላም ነው?
በረት ቢኖር ላም የለበት…
ላሙ ቢኖር እረኛ አልባ፥
ከተኩላ ጋር የሚያደባ፤
…የለም በረት”
– “ኡፍ… አታድርቀኝ፥ ይሁንልህ የመሰረት”
“የትኛው መሰረት እማ?
ያንኛው መሰረት፣ ሲፈርስ ያላየሽው?
ባሎችሽ ሲንዱት፥ ቆመሽ ያፋረስሽው?
ፈርተሽ ያላስጣልሽው?
በተበላ ቁማር፥…
ስጋ፣ ደም፣ ቆዳ፣ አጥንት የተገበረለት?
ያንኛው መሰረት?”
– “ኡፍ… ቀጥል”
“እሺ”
– “እሺ”…
“አንዲት ጋለሞታ…”
– “እሺ”
“ብዙ የወለደች፥ ብዙ መንታ መንታ፥
ልጆቿን የጣለች፣ ብዙ ባል አግብታ፥
ይህን ያህሉ ሞተው፣ ይህን ያህሉን ፈትታ፥
ይህን ያህሉ ታስረው፣ ይህን ያህሉን ረስታ”
– “እሺ”
“ከርታታ ልጆቿ…
በባሎቿ ክፋት ተማረው ሲነጉዱ፥
ማደሪያ ፍለጋ፥ ከቤት ሲሰደዱ፥ ጎረቤት ሲሄዱ…”
– “እሺ”
“ሲሄዱ ሲሄዱ ሲሄዱ…
ሲሄዱ ሲሄዱ ሲሄዱ…”
– “እሺ…”
“ሲሄዱ ሲሄዱ ሲሄዱ…”
– “እሺ”
.
.
“ተረቴን መልሱ” እንዳልላት፥ ፈራሁ…
ዳቦ የላት ከእጇ፥
አፌ እንዳይታበስ፥ በእግረ ሙቅ በዱላው፥
በጉልቤ ባሎቿ…
እናም ዝም ብዬ፥
“ልጆቿ በየመንገዱ፥
ሲሄዱ…
ሲሄዱ…
ሲሄዱ…
ሲሄዱ…



.
.
.
/ዮሐንስ ሞላ/

የወዳጅ ኀዘን…?!

ሜሪ አርምዴ፥ “ኧረ የጁ የጁ” በሚለው ሙዚቃዋ ላይ፥…. “አይገድልም መስሎሀል የወዳጅ ኀዘን?!” ትላለች…. እውነቷን ነው፤… – ይመስለኛል…. የወዳጅ ኀዘን ይገድላል። በመበደሉ ምክንያት ሰዎች/ተበዳዮች አምርረው ያለቀሱበት ሰው አይሳካለትም። የቆመ፣ የገደለ፣ ያሰቃየ፣ ያሰረ… ቢመስለውም አይዘልቅም። …ለዚያም፥ ብዙ ጊዜ ኅሊናውን ቢንቅ እንኳን፥ ከቀልቡ ያለ ሰው በልቡም ቢሆን ግፍ ይፈራል።

አምላክ ግፍ ይቆጥራል። …በህሊና ቢስነቱና በጭካኔው ሰው ያቃሰተበት ሰው ዋጋውን ያገኛል፤ በተራው ያቃስታል። እዚያው በዚያው አይወራረድ እንጂ፥ እግዚአብሔር ይፈርዳል። እርግማን ያሽመደምዳል። …እግዚአብሔር በግፈኞች ፍርድ መጠን ፈርዶ፥ እግዚአብሔር መሆኑን እንዲያውቁ እንደሚያደርግም በትንቢት ተነግሮናል። …ያው ለሚያምኑት ነው! (የማታምኑ እምነት ማለት አመክንዮና ሀልዮት የማይደረድሩለት፣ ማረጋገጫ የማይሹለት እውቀትና ከራስ ጋር መስማማት ነውና፥ አትድከሙ። አለማመናችሁን እመኑትና፥ ይህን ባላየ ላሽ በሉት።) …በበኩሌ፥ እንዲህ ተነግሮኛልና እንዲህ አምናለሁ! እንዲህ ሲሆን ተመልክቻለሁና እንዲህ አውቃለሁ!

…ሆኖም ግን እግዚአብሔር ለሚፈርድ፥ ሰው ጣልቃ መግባት የለበትም። “ኧከሌ ዋጋውን አገኘ” በማለት ውስጥ፥ ‘እኔ ግን ያልጠፋሁት ስለምሻል ነው’ የሚል ያልተፃፈ መልዕክት ይነበባልና፥ ግብዝነት ምንም አይረባም። ግፈኛ ሰው/አካል ላይ የሆነው ሲሆን “እሰይ” ብለው በተመለሱበት ቅፅበት፥ ራስ ላይ የሚሆነውን አያውቁም። …“ስለዚህ እንደ ቆመ የሚመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ።” ~ (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 10:12) ተብሎ ተነግሮናልና፥ ደግሞ ስለሌላው አቋቋም እንከንና አወዳደቅ ከማውራታችን በፊት፥ የራሳችንን አቋቋም መሻልና ፅናት ብንመለከት መልካም ነው።
.
.
.
እግዚአብሔር ሁሉን የሚችል (omnipotent) እና ሁሉም ቦታ የሚገኝ፥ ምሉእ በኩልሄ (omnipresent) መሆኑን ባምንም፥ …በሳውዲ አረቢያ ግዛት ላይ የደረሰውን በደል ‘የእግዚአብሔር ቅጣት ነው/አይደለም’ አልልም። ይህን የማልለው አሁን በማልዘረዝራቸው ብዙ ምክንያቶችና ጥያቄዎችም የተነሳ ነው። …ያ ለምን እንደሆነ የሚያውቀው እግዚአብሔር ብቻ ነውና በአሰራሩ ላይ ጣልቃ አልገባም። ይልቅስ ጥያቄዬን ለባለቤቱ አሳስብ ዘንድ እመኛለሁ።

በእነርሱ ላይ በሆነውና ካለሀጢአታቸው በ“አባት እዳ ለልጅ” ብሂል ለሚጠፉና ለሚጎሳቆሉ ነፍሳት ግን አዝናለሁ። ተንፈራግጠው ራሳቸውን ማዳን ስለማይችሉ ህፃናትና አዛውንት (አስራ ምናምን ሚሊዮን የሚሆኑ) አዝናለሁ። በመካከሉ መጠጊያና መሸሸጊያ ለሌላቸው፥ ምናልባትም እርዳታ ቢያሻቸውና ቢደረግ ለኗሪና ለቤተዘመዱ ሁሉ ከተደረገ በኋላ ለሚደረስላቸው ስደተኞች (የተረፉ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ) አዝናለሁ። …ካለጥፋቱ ስለሚቀጣ ሁሉ ከልቤ አዝናለሁ። ይህ የስሜት ጉዳይ ነውና፥ ለትችትና ወቀሳ አይበቃም። ማዘን ባይቻል እንኳን ያዘነን ሰው ‘ለምን?’ ማለትም ጥቅም የለውም።

በጌቶችና በአሽቃባጮቻቸው ክፋት የተነሳ መላው አዲስ አበባ ላይ እንዲህ ያለ የተፈጥሮ አደጋ ቢደርስ እንደማልደሰት፥ እንዲሁ በዚያም አልደሰትም። ደግሞስ በዚያ ለመደሰትና፣ “እሰይ” ለማለት እኔ ማን ነኝ? “ጌታም እንዲህ አለው፦ አሁን እናንተ ፈሪሳውያን የጽዋውንና የወጭቱን ውጭ ታጠራላችሁ፥ ውስጣችሁ ግን ቅሚያና ክፋት ሞልቶበታል” ~ 11:39 የሉቃስ ወንጌል ….ታዲያ ለጥፋት ጎርፍ ከታዘዘ፥ እኛስ በየትኛው ንፅህናችን ነው የምንተርፈው?

በሌላው ጉስቁልና በመደሰትና፣ በመስፈር ግን፥ ማዘንና በዚያው መስፈሪያ መሰፈር ሊመጣም ይችላልና፥… “አቤቱ፥ እንደ በደላችን ሳይሆን እንደቸርነትህ”!
አሜን!!
.
.
.
P.S.
ለአንዳንድ ጥቃቅንና አነስተኛ ተሳዳቢዎች: ….እንግዲህ እኔ እንደመሰለኝ ነውና፥ “ለምን እንዲህ ይመስልሀል?” ማለቱ ጉንጭ ማልፋት ነው። ይልቅስ፥ እናንተ የሚመስላችሁ ከዚህ የተለየ ከሆነ፥ ሳትሳደቡና ሳትበሳጩ፥ በማክበር ከጎኑ ቁጭ አድርጉት። የሚማር የትም/ከማንም ይማራልና፥ ይመዝን ዘንድ እንዲረዳው አንፃር ይሆነዋል።

ኢአማኒ (atheist) ብትሆኑ ደግሞ፥ አለማመናችሁን በንግግርና የእኔን ማመን በመንቀፍና በንፅፅር (comparing and contrasting) ሳይሆን፥… ባለማመን ፀንታችሁና፥ በሕይወታችሁ ኖራችሁት አሳዩኝ።

ሰላም ለሁሉም!!

 

የወዳጅ ኀዘን…?!

ሜሪ አርምዴ፥ “ኧረ የጁ የጁ” በሚለው ሙዚቃዋ ላይ፥…. “አይገድልም መስሎሀል የወዳጅ ኀዘን?!” ትላለች…. እውነቷን ነው፤… – ይመስለኛል…. የወዳጅ ኀዘን ይገድላል። በመበደሉ ምክንያት ሰዎች/ተበዳዮች አምርረው ያለቀሱበት ሰው አይሳካለትም። የቆመ፣ የገደለ፣ ያሰቃየ፣ ያሰረ… ቢመስለውም አይዘልቅም። …ለዚያም፥ ብዙ ጊዜ ኅሊናውን ቢንቅ እንኳን፥ ከቀልቡ ያለ ሰው በልቡም ቢሆን ግፍ ይፈራል።

አምላክ ግፍ ይቆጥራል። …በህሊና ቢስነቱና በጭካኔው ሰው ያቃሰተበት ሰው ዋጋውን ያገኛል፤ በተራው ያቃስታል። እዚያው በዚያው አይወራረድ እንጂ፥ እግዚአብሔር ይፈርዳል። እርግማን ያሽመደምዳል። …እግዚአብሔር በግፈኞች ፍርድ መጠን ፈርዶ፥ እግዚአብሔር መሆኑን እንዲያውቁ እንደሚያደርግም በትንቢት ተነግሮናል። …ያው ለሚያምኑት ነው! (የማታምኑ እምነት ማለት አመክንዮና ሀልዮት የማይደረድሩለት፣ ማረጋገጫ የማይሹለት እውቀትና ከራስ ጋር መስማማት ነውና፥ አትድከሙ። አለማመናችሁን እመኑትና፥ ይህን ባላየ ላሽ በሉት።) …በበኩሌ፥ እንዲህ ተነግሮኛልና እንዲህ አምናለሁ! እንዲህ ሲሆን ተመልክቻለሁና እንዲህ አውቃለሁ!

…ሆኖም ግን እግዚአብሔር ለሚፈርድ፥ ሰው ጣልቃ መግባት የለበትም። “ኧከሌ ዋጋውን አገኘ” በማለት ውስጥ፥ ‘እኔ ግን ያልጠፋሁት ስለምሻል ነው’ የሚል ያልተፃፈ መልዕክት ይነበባልና፥ ግብዝነት ምንም አይረባም። ግፈኛ ሰው/አካል ላይ የሆነው ሲሆን “እሰይ” ብለው በተመለሱበት ቅፅበት፥ ራስ ላይ የሚሆነውን አያውቁም። …“ስለዚህ እንደ ቆመ የሚመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ።” ~ (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 10:12) ተብሎ ተነግሮናልና፥ ደግሞ ስለሌላው አቋቋም እንከንና አወዳደቅ ከማውራታችን በፊት፥ የራሳችንን አቋቋም መሻልና ፅናት ብንመለከት መልካም ነው።
.
.
.
እግዚአብሔር ሁሉን የሚችል (omnipotent) እና ሁሉም ቦታ የሚገኝ፥ ምሉእ በኩልሄ (omnipresent) መሆኑን ባምንም፥ …በሳውዲ አረቢያ ግዛት ላይ የደረሰውን በደል ‘የእግዚአብሔር ቅጣት ነው/አይደለም’ አልልም። ይህን የማልለው አሁን በማልዘረዝራቸው ብዙ ምክንያቶችና ጥያቄዎችም የተነሳ ነው። …ያ ለምን እንደሆነ የሚያውቀው እግዚአብሔር ብቻ ነውና በአሰራሩ ላይ ጣልቃ አልገባም። ይልቅስ ጥያቄዬን ለባለቤቱ አሳስብ ዘንድ እመኛለሁ።

በእነርሱ ላይ በሆነውና ካለሀጢአታቸው በ“አባት እዳ ለልጅ” ብሂል ለሚጠፉና ለሚጎሳቆሉ ነፍሳት ግን አዝናለሁ። ተንፈራግጠው ራሳቸውን ማዳን ስለማይችሉ ህፃናትና አዛውንት (አስራ ምናምን ሚሊዮን የሚሆኑ) አዝናለሁ። በመካከሉ መጠጊያና መሸሸጊያ ለሌላቸው፥ ምናልባትም እርዳታ ቢያሻቸውና ቢደረግ ለኗሪና ለቤተዘመዱ ሁሉ ከተደረገ በኋላ ለሚደረስላቸው ስደተኞች (የተረፉ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ) አዝናለሁ። …ካለጥፋቱ ስለሚቀጣ ሁሉ ከልቤ አዝናለሁ። ይህ የስሜት ጉዳይ ነውና፥ ለትችትና ወቀሳ አይበቃም። ማዘን ባይቻል እንኳን ያዘነን ሰው ‘ለምን?’ ማለትም ጥቅም የለውም።

በጌቶችና በአሽቃባጮቻቸው ክፋት የተነሳ መላው አዲስ አበባ ላይ እንዲህ ያለ የተፈጥሮ አደጋ ቢደርስ እንደማልደሰት፥ እንዲሁ በዚያም አልደሰትም። ደግሞስ በዚያ ለመደሰትና፣ “እሰይ” ለማለት እኔ ማን ነኝ? “ጌታም እንዲህ አለው፦ አሁን እናንተ ፈሪሳውያን የጽዋውንና የወጭቱን ውጭ ታጠራላችሁ፥ ውስጣችሁ ግን ቅሚያና ክፋት ሞልቶበታል” ~ 11:39 የሉቃስ ወንጌል ….ታዲያ ለጥፋት ጎርፍ ከታዘዘ፥ እኛስ በየትኛው ንፅህናችን ነው የምንተርፈው?

በሌላው ጉስቁልና በመደሰትና፣ በመስፈር ግን፥ ማዘንና በዚያው መስፈሪያ መሰፈር ሊመጣም ይችላልና፥… “አቤቱ፥ እንደ በደላችን ሳይሆን እንደቸርነትህ”!
አሜን!!
.
.
.
P.S.
ለአንዳንድ ጥቃቅንና አነስተኛ ተሳዳቢዎች: ….እንግዲህ እኔ እንደመሰለኝ ነውና፥ “ለምን እንዲህ ይመስልሀል?” ማለቱ ጉንጭ ማልፋት ነው። ይልቅስ፥ እናንተ የሚመስላችሁ ከዚህ የተለየ ከሆነ፥ ሳትሳደቡና ሳትበሳጩ፥ በማክበር ከጎኑ ቁጭ አድርጉት። የሚማር የትም/ከማንም ይማራልና፥ ይመዝን ዘንድ እንዲረዳው አንፃር ይሆነዋል።

ኢአማኒ (atheist) ብትሆኑ ደግሞ፥ አለማመናችሁን በንግግርና የእኔን ማመን በመንቀፍና በንፅፅር (comparing and contrasting) ሳይሆን፥… ባለማመን ፀንታችሁና፥ በሕይወታችሁ ኖራችሁት አሳዩኝ።

ሰላም ለሁሉም!!

 

ቅጥልጥልጥል… :(

የ“ምንም አልሆንኩም” (I’m alright…and everything is so) ስሜት ፈጠራ በሽታ (pseudologia fantastica?) ተጠቂዎችን ሳይ ያስቀኛል። እየተናደድኹም ቢሆን እስቃለሁ። ….ብዙውን ጊዜ ስለሆኑት ነገር ሳይሆን ለሌላው ስለሚመስሉት ነገር ነው የሚጨነቁት። (“ደህና ነኝ” የሚለውን ስሜት ለመትከል መጣሩም የሚመጣው ደህና ካለመሆን ይመስለኛል።) ስለሆነም፥ ያልሆኑትን ለመምሰል በብዙ ይጨነቃሉ። በብዙም ይቀባባሉ። በመደዳም ይዋሻሉ።

መጣላታቸውን ሀገር ምድር ያወቀባቸው ጥንዶች ጥቂት ሲስማሙ፣ (ወይም ሳይስማሙ በፊት) ሀሜቱን ሲፈሩት “ወረኛም ያውራ ሀሜት ይደርድር፥ እኛስ ሆነናል ፍቅር በፍቅር“ ዓይነት ይዘት ያላቸው ዜማዎችን ለማቀንቀን ማንም አይቀድማቸውም። …ከጠብ መልስ ያለውን የመፋቀር ጊዜ እንኳን ሳያጣጥሙ፥ ‘ታርቀናሉን’ ለመንዛት ነው የሚቸኩሉት። …ባይታረቁ እንኳን፥ የምንም አልሆንኩም ስሜቱን ለማቀንቀን ላይ ታች ይላሉ።

ያልተገባ ነገር እንዳደረጉ የሚያውቁና፥ በዚያም ድርጊታቸው ሰው ያወገዛቸው ሰዎች “ሆነ ብዬ ነው የሰራሁት፥ እንጂ ሁሉም ሰላም ነው” (I did it intentionally; otherwise, everything is okay) የሚል ስሜት መፍጠር ይፈልጋሉ። ይህንንም፥ በ“ካፈርኹ አይመልሰኝ” ዘዬ፥…. ወይ ያልተገባውን ነገር በመደጋገም፣ ወይ ደግሞ ስለርሱ ነገር ፈታ ብለው በመተንተንና ማብራሪያ በመስጠት፥ የስነ ልቡና ጨዋታ ለመጫወት ይጥራሉ።

….በበሽታ ማቅቆ ከዛሬ ነገ ይሞታል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረ ሰው፥ ምናልባት ወዳጅ መሳይ ባላጋራዎቹን ማበሳጨት ቢፈልግ (ምናልባት በህመሜ ምክንያት ታምቻለሁ፣ ተደስተዋል ወይም ተገልያለሁ ብሎ ሲያስብ) እንዲሁ የሞት ሞቱን ተነስቶ ባልባስ ያሸበርቅና ድምፁ እንዲሰማ ከፍ አድርጎ ይጫወታል፣ ይጣራል፣ ይበሳጫል። – ጮክ ብሎ! …በአሽሙር ‘ተሽሎኛል (I’m alright) ይብላኝ ለእናንተ’ መልዕክቱን ለማስተላለፍ ይጥራል።

ምርምር ባላካሄድም፣ ወይም የጥናት ወረቀቶችን ባላነብም፥… እንዲያው በደመነፍስ እና ከልምድ ተነስቼ ስገምተው፥ የዚህ በሽታ ተጠቂዎች በብዛት የታችኛው ክፍል ሰዎች ይመስሉኛል። የታችኛው ማለቴ፥… አለ አይደል? – የታዕታይ ስሜት (inferiority complex) የሚያነጫንጫቸው…. በሰላሙ (normal condition) ወይም በላዕላይነት ስሜት (superiority complex) መንጫጫት ወቅት፥ በግልፅ ማሳየት እያለ፥ ፈጠራው ይቀንሳል። – መሰለኝ!

ይህን ሁሉ የሚያስቀባጥረኝ ኢቲቪ ነው። ከስንት ጊዜ በኋላ፣ ለያውም በክፉ አጋጣሚ፥ ዛሬ ኢቲቪ ባይ የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩን ዶ/ር ቴዎድሮስንና የአረብ እንግዶቹን በብዛት ተመለከትኹኝ። የዶ/ር ቴዎድሮስ ስምና ምስል በየዜናው (4 ወይም 5 የሚሆኑ ዜናዎች ላይ) ስመለከት የ“ጓዶች፥ ተረጋግተናል… ወረኞች ወደየቦታችሁ“ ዓይነት መልዕክት እንዳለው ገመትኹኝ። (not taking it personally!, but feeling it as a failed mockery &mocking back on it. Hehehe….)

ዶ/ሩ አንዴ አረብ ሲቀበሉ፣ አንዴ የቤተሰብ ምጣኔ ኮንፈረንስ ላይ ንግግር ሲያደርጉ ታዩ። ግን በጤነኛ አእምሮ የህዝቡ ጉዳይ ባያሳስባቸው እንኳን፥ የህዝቡ ስሜት ስለሚያስጨንቃቸው ተኝተው የሚያድሩ አይመስለኝም። በተለይ እርሳቸው፥ ከትዊተር ገፃቸውም የምረዳው ከህዝብ ጋር የመቀራረብ የከሸፈ ዝንባሌያቸውን ነው። (መክሸፉ የተሰማኝ ከሰሞኑ ነው) …(Hmm, but seriously, how easy is to pretend ‘its alright’, while it is not? ….if it is felt really, how easy is seeing-not a psychiatrist? – curious )

ሌላው የ’we’re alright…and won’t broke up’ ስሜት ያየሁት ደግሞ አረቦቹን ስመለከት ነው። ከቴዎድሮስ አድሀኖም ጋር የነበሩት ሲገርመኝ፣ የቢዝነስ ዘገባው የመጀመሪያ ዜናም ከአረብ ኤሚሬትስ ጋር ስለተደረገ ስምምነት/ ወይም ፍላጎት (or whatever) የሚያወራ ነበር። እዚያ ላይ ደግሞ አብረው የታዩት ፕሬዝዳንቱ ናቸው። (ከመገረሜ የተነሳ የወሬዎቹን ይዘት በጥልቀት ልብ አላልኹምና አትታዘቡኝ።)

…ምናልባትም ከፕሬዝዳንቱ ጋር የታዩት፥ ከሚንስትሩ ጋር የታዩት የቀደሙት አረቦች ይሆናሉ። እንዲያ ከሆነ ደግሞ… አንዴ የሆነውን ደግሞ በማሳየት የ“ደህና ነኝ”ኡን ስሜት፥ ወደ “በጣም ደህና ነኝ” ያሳድገውና፥ ሳቄን ከፍ ያደርገዋል።) …እኔማ ወላ፥ ለገፅታ ግንባታው የመጡ ተዋናዮች እንደሆኑ ተሰምቶኛል። (እነ ፀጉር ሰንጣቂዎች፥ ተሰምቶኛል እንጂ ነው አላልኹም። መቼስ የሚሰማኝ አማክሮኝ ስላልሆነ አትፍረዱብኝማ።)

በተቃራኒው ሲታይ ደግሞ፥ ነገሩ ሁሉ፥ “እናንተ እኮ ዝም ብላችሁ ነው እንጂ፥ እኛ ታምመናል።” ዓይነት የውሸት ስሜት ፈጠራ በሽታ (factitious disorder) ተጠቂነት ውጤት ይመስላል። እንጂ ሰው በሰላሙ እንዴት የሚያስገብረውንና ሰጥለጥ አድርጎ የሚገዛውን ሕዝብ ያቆስላል? …መቋሰሉ ደግሞ ሉአላዊነትን አሳልፎ በመስጠትና ለሌሎች በማሸርገድ ዋጋ መሆኑን ማሰብ ደግሞ ከቁስሉ በላይ ያማል።

አቶ ሽመልስ ከማልማ ‹‹የሳውዲ መንግስት በአገሩ የአሰሪና ሰራተኛ ህግ መሰረት እርምጃ የመውሰድ ሉአላዊ መብት እንዳለው እንገነዘባለን›› ብለው የዓመቱን አስገቡልን። ኧረ እኔስ፥ ወረድ ብለው ‹‹የኢትዮጵያ መንግስት በአገሩ የፀረ ሽብር ህግ መሰረት ሰልፍ የመከልከልና የጉልበት እርምጃ የመውሰድ ሉአላዊ መብት እንዳለው እናስገነዝባለን።›› ይላሉ ብዬም ፈርቼ ነበር።

ጨዋታው ይቀጥላል! ….ግድ የለሽነታቸውም! ….መቃጠላችንም! መቼስ ማልጎደኒ!

…ሰው ግን ወዶ አይደለም ለካ የባለጌ ነገር የሚሳደበው?!