አልወዳለሁ!

ንፋስ እወዳለሁ፤…
ንፋስ ማን ይጠላል?images
ከገለባ ጋራ መውደድ እንዳይደረጅ
የበራሮች ፍቅር እንዳያንቦጃቡጅ፥
እንዳያንጎላጅጅ፣
እንዳያሳር እግር፣ እጅ፤
በጊዜ ጠራርጎ ይወለውልና፥
ብርቱውን ያስቀራል፤
አቁሽሹን አብርሮ፥
ቋሚውን ያስበራል፤
አፍዝዙን ወልውሎ፥
ጥንኩሩን ያደምቃል።
ንፋስ ማን ይጠላል?!

ንፋስ እጠላለሁ፤…
ንፋስ ማን ይወዳል?
ገለባ፣ ልጣጩን፣ ጥራጊውን ሁሉ፥
ኬ’ትም ደጃፍ ዘግኖ፥
ኬ’ትም ሰፈር ለቅሞ፥04a227964828823e18db88ce9e1b7247
ሰውነት ላይ ጭኖ፥
ገላን አሸክሞ፥
ብርቱን ያቆሽሻል፥
ደማቁን አዳክሞ፤
መልኩን ይጋርዳል፥
ብርሃኑን ጨላልሞ።
ንፋስ ማን ይወዳል?!

ሲበሩ፣ ሲያበሩ፥
ተገትሬ ቁሜ እቀዣበራለሁ፥
ንፋስ አልወዳለሁ።

/ዮሐንስ ሞላ/

Note: Photos are found from internet.

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s