አንድ አብሮ አደጋችን፣ እሱ ቢያጠፋው ኖሮ እናቱ ሳትቀጣው የማትቀርበት ነገር፥ እናቱ ስታጠፋ ተመልክቶ (ለምሳሌ፥ ብርጭቆ ሰብሮ ነበር በሉት። እናቱ ለቅጣት እጇን ባታነሳበት እንኳን “እያየህ አትሄድም? ደንባራ። እቃዎቹን እኮ ፈጀኻቸው።” ልትለው ትችላለች)፥ “እሺ አንቺንስ ማን ይምታሽ? እግዚአብሔር ይምታሽ።” አላት አሉ። …ልጅ ነበርና፥ እናቱን በእግዚአብሔር ለማስቀጣት መፈለጉ ከማሰላሰል ብቃቱ የመጣ ነበርና ተደናቂ ነገር ሆኖ እስካሁን ድረስ ይታወሳል። እኔም በምክንያት አስታውሼ አመጣሁት።

ከዚህ ጋር ያለውን ጽሁፍ፥ በመስቀል አደባባይ ስትተላለፉ አይታችሁት ታውቁ ይሆናል። (ከኤግዚቢሽን ማዕከል ፊትለፊት አስፓልቱን ተሻግሮ ካለ ህንጻ ላይ ከተሰቀሉ መፈክሮች መካከል አንዱ ነው።) ሳየው ኖሬ፣ ዛሬ ድንገት አስፓልት ስሻገር ተገጣጥመን፣ በእጅ ስልኬ ፎቶ አነስቼው ነው ያመጣሁት። እንደሚነበበው፥ ጽሁፉ “የሃይማኖታችን ዋስትና ህገ መንግስታችን ነው። ህገ – መንግስታችን ይከበር!!” ነው የሚለው። ይህን ጽሁፍ ባየሁ ቁጥር የዞን 9 ወዳጆቼ ትዝ ይሉኛል።

እንደሚታወሰው፥ ከበይነ መረብ ዘመቻዎቻቸው መካከል “ህገ መንግስቱ” ይከበር የሚለው ይገኝበታል። (ከዚህ ዘመቻ በቀር፥ በሌሎቹ ሁሉ ተሳትፌ ነበር። መሳተፍ ያልመረጥኩት ለራሴ በቂ በሆነ ምክንያት ነው።) በምርመራ ወቅትም፥ ሲዘልፏቸው “ህገ መንግስቱ ተከብሮ ሳለ ምን ስለሆናችሁ ነው ይከበር የምትሉት?” የሚል ጥያቄ ተሰንዝሮባቸው ነበር። (እንደሰማሁት ቃል በቃል አልጻፍኩትም።)

ታዲያ ከዚያ ጊዜ አንስቶ፥ ይህን የለጠፈው/ያስለጠፈው ሰው ምን ቆርጦት ነው “ህገ መንግስታችን ይከበር” የሚለው?

ማንስ ነው ህገ መንግስቱን የሚያከብር የሚያስከብረው?

ህገ መንግስቱ በደንብ ይታወቅና ይከበር! በደንብ መታወቁ፥ አከባበሩ ላይ ባለድርሻዎች የሚኖራቸውን ሚና ግልጽ ያረጋልና፥ መጀመሪያ በደንብ ይታወቅ። ከዚያ ይከበር! (አሃ! ይከበር ስንል ግን፥ ቀን ተቆርጦለት የህገ መንግስት ቀን የሚባለውን አይደለም።) ህዳር 29 ብቻ ሳይሆን፥ ከህዳር 30 – ህዳር 28 ድረስም ህገ መንግስቱ ይከበር!

11692578_797852720335763_2642146807227495581_n

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s