እሾህ ልነቅልበት፣ እባጭ ላፈርጥበት
ያገባሁት እሾህ፥
ህመሜን ሊነቅል፣ ሊያሳርፈኝ ቀርቶ፥
ምዝምዝ አደረገኝ፣ በሽታዬ ጸና፤
እርሱው ተሰክቶ፥
ሌላ እሾህ ፈለገ ‘ሚያወጣው ጎትቶ፣
ኀሠሣ ሰላሜን፥ ከበጣሁት ቆዳ፥
ሆኖብኝ ሌላ ዕዳ።

/ዮሐንስ ሞላ/