በተለይ ስለዮናታን…

10583842_558489044309215_4067362789194959249_n“ሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊውን ጨምሮ አራት አባሎቹን ማሰናበቱን አስታወቀ” መባሉን ተከትሎ፥ በተለይ ስለዮናታን…

ራሱን (ከጥር 2 በፊት)፥ ከፓርቲው ማግለሉን እስከገለጸበት ጊዜ ድረስ፥ በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ስር፥ በአባልነት እና በሕዝብ ግንኙነት ኃላፊነት ጊዜው፣ ፓርቲውን ታምኖ ሲያገለግል የነበረው ዮናታን፥ እስር ቤት ውስጥ ባለበት፣ ራሱን መከላከል እና ጉዳዩን ተንትኖ ማስረዳት በማይችልበት ሁኔታ ውስጥ ሆኖ (እንደማይጎበኝ ይታወቃል) የፓርቲውን ውሳኔ ሲሰማ ምን ይሰማው ይሆን?

ሲጀመር ውሳኔው አግባብ ነው? “ውሳኔ” ለመባል ይበቃል? ቀድሞ ዮናታን “ከፓርቲው ራሴን አግልያለሁ” ካለ በኋላ፥ “በዚህ በዚህ ምክንያት ከፓርቲው ተባረሃል” ማለትስ ፓርቲውን ከማስገመትና ለከሳሾቹ ግብአት ከመሆን ውጭ ጥቅም ይኖረዋል? አሳልፎ መስጠትስ ከዚህ አይሻልም?

ዮናታን ስለውሳኔው ለፓርቲው በደብዳቤ ማሳወቅ አለማሳወቁን ባላውቅም፥ በፌስቡክ በኩል ራሱን ከፓርቲው ማግለሉን ከገለጸ በኋላ፣ በፓርቲው ስራ ላይ እንደማይሳተፍ እሙን ነው። (ውሳኔውን በሰሙበት ወቅት፥ እንደ ቀልጣፋ አባልነቱ፣ ጉዳዩ ላይ ተወያይቶ መተማመን ላይ ለመድረስ አለመጣራቸውም፥ ‘ለአባላት ግድ የለሽ በመሆን’ ረገድ ያስገምታል።) ይህም ማለት፥ ሰማያዊ ፓርቲ፥ ከውሳኔ እና አካሄድ ለውጥ ባሻገር በፓርቲው ስራ ላይ ተሳትፎ ባለማድረግ ምክንያት አባላቶቹን ሊያሰናብት የሚችልበት የመተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ ሳይኖረው አይቀርም። (ከሌለው ይህም ፓርቲውን የሚያስገምት ሌላ ጉዳይ ነው።)

ታዲያ በስራ ገበታ ላይ ባለመገኘት ምክንያት መሰናበት ያለበትን ሰው፥ በገዛ ጊዜው ቀድሞ ፓርቲውን መሰናበቱን የገለጸን ወጣት “ዮናታን በማኅበራዊ ድረ ገጽ ላይ የታሪክና የጎሳ ጥላቻ ያላቸው ቅስቀሳዎችን በማድረግ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብና የተለያዩ የአገሪቱን ቀደምት መንግሥታት ታሪኮች ያጎደፈ፣ ለጥላቻ የሚያነሳሳ፣ በሕዝብ መካከል የባህል መከባበር እንዳይኖር የጥላቻ ቅስቀሳ አድርጓል።” ብሎ ምክንያት ማቅረብ በምን ዓይነት ሚዛን ነው ልክ የሚሆነው?

1. ሰማያዊ ፓርቲ የአቃቤ ህግን የክስ መዝገብ የማጠናከርና በምስክርነት የመቅረብ ሚና ኖሮት ይሆን? ወይስ በመንግስት ፊት ሞገስን ፍለጋ? ወይስ ‘ሰማያዊነትን’ ሰበካ እና ገጽ ግንባታ?

2. ፓርቲውን መልቀቁን ስለተናገረ ሰው፥ ባለፈው “አባላቶቼ በግፍ ታሰሩ” ብለው እንደ አቋም መግለጫ ዓይነት ደብዳቤ ጽፈው ስም ሲዘረዝሩ የእሱንም ስም መጥቀስ (እዚህ ሲዞር የነበረ ደብዳቤ ነበር)፣ አሁን ደግሞ “ከፓርቲው አባርሬዋለሁ” ማለት ምን ማለት ነው?

3. ዮናታን ‘የፓርቲው ደንብ ከእንግዲህ የእኔ ደንብ አይደለምና፣ የፓርቲ አይደለሁም’ ብሎ በራሱ መንገድ መኖሩና የተሰማውን ሲገልጽ መቆየቱ፥ …የታሪክና የጎሳ ጥላቻ ያላቸውን ቅስቀሳዎች ማድረግ፣ ታሪክ ማጉደፍ፣ ለጥላቻ ማነሳሳት እና በሕዝብ መካከል የባህል መከባበር እንዳይኖር የጥላቻ ቅስቀሳ ማድረግ… የሚሆነው በማን ተመዝኖ ነው?

4. ሚዛኑም፣ አስተያየቱም፣ ውሳኔውም ልክ ናቸው ብለን እናስብና… ዮናታንን ፓርቲውን ለመልቀቅ እስከማስወሰን ያደረሰውን ምክንያት መመርመር እና እንደፓርቲ ከእርሱ ውሳኔ እና ከነባራዊ ሁኔታዎች ለመማር መጣር አይቀድምም ነበር? የተሻለስ አይጠቅምም ነበር?

5. ያሉት አባላቱስ ይህን ውሳኔ ሲሰሙ በእጃዙር ጭቆና ውስጥ አይውሉም? እንደ ‘ሀሳቤን ብቀይር እንዲህ ይሆንብኛል’ ዓይነት ያለ፥ ‘ስጋት ወለድ ፍርሀት’ ውስጥ መኖር?

6. አዳዲስ አባላትስ ወደ ፓርቲው ይሳባሉ? ሰላማዊ ትግልን በተመለከተስ የሚያጠላው መጥፎ ነገር አይኖርም? (ካለፉ ታሪኮች ስንመለከትም እንደዚህ ዓይነት *ማሳጣቶች* እና ለከሳሾች መጠቀሚያ መሆን፥ የተለመዱ ስለሆነም ጭምር)

ይህኔ ነው፥ “ነጻነትን የማያውቁ ነጻ አውጪዎች” ማለት!

ዜናውን ለማንበብ ይህን ይጫኑ።

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s