12936736_1353244648025346_6022529115159645969_nድራማው የቀን ቅኝት ነው፤ “ማለቂያው ሩቅ ነው” ስልሽ፥ ወዳጄ!

ከ15 ሚሊየን ሕዝብ በላይ በተራበበት አገር ውስጥ፥ ከአንድ ሺ ሚሊየነር ገበሬዎች ሸልመናል ይባልልኛል። ታዲያ ይኼ በአንድ ክልል ውስጥ ነው። የሌላውን የክልሉ ኮካዎች ሀላፊ ሰብስቦ ሲሸልመው ወሬውን እንሰማለን።

እንበል (let’s assume):

ያን ያህል ሚሊየነር ገበሬዎች አሉ። ሁሉም ያላቸው የሀብት መጠን አንድ ሚሊዮን በነፍስ ወከፍ ብቻ ነው እንበል። አንድ ሺህው በጋራ 1 ቢሊዮን ብር ሀብት ይኖራቸዋል ማለት ነው።

ታዲያ ይሄ ሁሉ ሚሊየነር ገበሬ ሞልቶ ረሀቡ እንዴት ተከሰተ?

“ድርቁ” አላልኩም። ድርቁ የተፈጥሮ ጉዳይ ነው። ዝናብ ሲመጣ፣ ዝናብ ሲሄድ የሚሆን ነገር ነው። ረሀቡ ግን ክፉ ቀንን አስቦ ምግብ ያለማስቀመጥ ውጤት ነው።

በአንድ አካባቢ ይህን ያህል ሚሊየነር ገበሬዎች አሉ ማለት፥ እንደከተማ ለሙስና እና ለዝርፊያ የተመቻቸ ሁኔታ ስለማይኖር፣ ኑሮው ይቀራረባልና የተቀሩት በብዛት በሺዎች የሚቆጠር ሀብት ይኖራቸዋል።

የኑሮ መሻሻል እና የሀብት መብዛት ደግሞ የአስተሳሰብ አድማስንም ይወስናልና (and the other way round) እንዴት ይሄ ሁሉ ሰው “ለነገ” ብሎ የማስቀመጥ ስነልቡና ሳይኖረው ቀረ?

እሺ እሱም ይቅር፥ በቀዬው፣ በክልሉ ይህን ያህል ሰው ሲራብ፥ ገበሬው ራሱ ቢያዋጣ ችግሩን/ገመናውን እዚያው ለዚያው ይሸፍነው አልነበር?

እሺ ይኼም ይቅር፥ “ወጧ እንዳማረላት ሴት” የሀላፊዎቹ “እዩኝ፣ ስሙኝ” ምንድን ነው?

ለሽልማቱስ ስንት ወጣ?

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s