“…”

የሕዝብ ጩኸት ቢገፋ፣
የንጹህ ሰው ደም ቢደፋ
‘ምድር’ ሲባል ርቆ መጥቆ
ሰማያቱን ሰነጣጥቆ፥
ይጮኻል በልዩ ግርማ፣
ይሰማል በእዮር፣ ራማ፤
የሰው ስጋ ተፈትቶ፣
አይቀርም በብላሽ ከቶ፣
የኀዘን መቀነትን ፈትቶ፣
ዋይታ ነዝቶ፣ ዕንባ አራጭቶ፤
 
ከበደል ጋር ተመዝኖ፣
የክብሩን አክሊል ጭኖ፣
ከሰማይ ምኩራብ ዳምኖ፣
ዶፍ ይዘንባል
ለገፊዎች መአት ሆኖ፣
ለተገፊ ምህረት ገንኖ፤
 
ንጹሕ ቢወድቅ ሺ ይነሳል፣
ሺ ያቆማል፣ ሺ ይጠራል፤
ንጹሕ ቢጮህ ሺ ያነቃል፣
ሺ ይጣራል፣ ሺ ይሰማል፤
ንጹሕ ደምቶ ሺው ፀአዳ፣
ተሸላልሞ በፍቅር ዕዳ፤
 
የንጹሕ ደም ከእንባ ገጥሞ፥
ሰማየ ሰማያት ከርሞ፣
ወደ ምድር ሲከነበል፣
ሺ ይጠርጋል፣
ሺ ያጸዳል፤
ሺ ያቀናል፣
ሺ ያሰምጣል…
 
ወዮ ላንተ ለገዳዩ…
ግዳይ ጥለህ ስትጨፍር፥
ለሚረግጥህ ተከታዩ፣
ያፈራኸው በክፋትህ፣
ያቀናኸው በግፋትህ!
 
የበደል ጽዋህ ሲሞላ፣
ትንሳኤው ሲበሰር የሰው
በሀሴት ፋሲካው ሲበላ፣
አንተ ትኖራለህ ወድቀህ፣
ተዘርረህ በሞት ጥላ።  
 
/ዮሐንስ ሞላ/

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s