ህግ እንዳከበረ ሰው ለመመጻደቅ አይደለም መቼም። ግን ሌሎች ትዕዛዛቱን ሲጥስ ስለኖረ፣ ከምዕመኑ እኩል “ንስሀ ግባ” ብሎ መወትወት ቢቀር፣ በዘርና በሀይማኖት ለያይቶ ሊደላደል እየዳከረ፣ በጠራራ ፀሐይ ሕዝብን እንደጤፍ ሲቆላና እንደምንም ሲያራግፍ፣ ክቡር ሰውነትን ባለቤት እንደሌለው ሲያንገላታ ባላየ ባልሰማ ኖረው (ለእግዚዮታ እንኳን ጥሪ ማድረግ አንድ ነገር ነበር)….
“ለቀደሙት አትግደል እንደተባለ ሰምታችኋል፤ የገደለም ሁሉ ፍርድ ይገባዋል እኔ ግን እላችኋለሁ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል፡፡” ማቴ. 5፡ 21-22 የሚለውን ትዕዛዝ ጠቅሰው ያላወገዙትና ጠብመንጃውን እንዲዘቀዝቅ ስለነፍስ ያልወተወቱት አካል፣ ሲጨንቀው “ኑ አማልዱኝ… ሕዝብን ዐይኑን ያዙልኝና ማሞኘቴን ካቆምኩበት ልቀጥል።” ሲል…
“ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።” ~ 1.ቆሮ.6: 19-20
“በዋጋ ተገዝታችኋልና የሰዎች ባርያ አትሁኑ” ~ 1ቆሮ.7፡23
“እርሱ ከጨለማ ሥልጣን አዳነን፥ ቤዛነቱንም እርሱንም የኃጢአትን ስርየት ወዳገኘንበት ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግሥት አፈለሰን።” ~ ቆላ.1፤13-14
“ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲህ ልጅ ነህ እንጂ ባሪያ አይደለህም፤ ልጅም ከሆንህ ደግሞ በክርስቶስ የእግዚአብሔር ወራሽ ነህ።” ~ ገላ.4:7
እና ሌላም ተብሎ የተነገረውን፣ ‘በክርስቶስ ክርስቲያን ተብለሀልና ሌሎች አማልክት አይሁኑልህ’ እያሉ ሲሰብኩት የኖሩትን ሕዝብ፣ ለመሸምገል ማሰቡ እንደምን ቀለላቸው?
ለነገሩ፣ ጥላሁን ገሰሰ ሞቶ ያኔ የነበሩት ጳጳስ ለቅሶ ቤት ሊያጽናኑ ሄዱ ተብሎ ወሬ ሲነገር፣ ጥሌን ብንወደውም፣ ስለዘላለማዊ ሕይወት ለመስበክ ሜዳና ፈረሱ ገጠሙላቸው ብለን ኢቲቪው ላይ ቸክለን ስንሰማ “ጥላሁን አልሞተም። ቤተክርስቲያናችን ሞተ የምትለው ምንም ሳይሰራ ያለፈን ሰው ነው…” ምናምን ብለው ያሸማቀቁንንም አንረሳውም።
እንደአቡነ ጴጥሮስ ‘ጽአ እርኩስ መንፈስ!… ሕዝቤን ልቅቅ’ ብሎ ጋንጩራቱን ጭራ የሚያስበቅል አባት እንናፍቃለን። ምህረቱ ለዘላለም ይሁን!!
የሀይማኖት ነፃነት ይከበር!
!
#Ethiopia #StopKillingCivilians