ብሩን ራሱን ነው እንዴ አብስለው ሚበሉት?

መንግስታችን፥ ዘመኑ አላመች ብሎት እንጂ፣ በዚህ አያያዙ በይፋ የባሪያ ንግድ ሁሉ ቢጀምር አይበቃውም። (ያው ከሳውዲ ጋር ያለው ውል ሳይረሳ። …የነውራቸው ብዛት እኮ፥ ከሳውዲ ጋር እየተዋዋሉ፣ ከአውሮፓ ሕብረት ጋር ስደተኞች እንዳይሄዱ ብለው ብር ይቀበላሉ።) ብሩን ራሱን ነው እንዴ አብስለው ሚበሉት?
 
“ታንዛንያ ከጅቡቲ፣ሱዳንና ኬንያ በመቀጠል ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የምታገኝ አራተኛዋ አገር ትሆናለች። …ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀንድ ባሻገር ሩዋንዳና ብሩንዲ ለመሳሰሉ በጣም ውድና ታዳሽ ያልሆነ ኃይል ለሚጠቀሙ አገራት እንዲሁም ለሰሜን አፍሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅና አውሮፓም የኤሌክትሪክ ኃይል የማቅረቡ ዕቅድ አላት።” ….ዜናው የኢዜአ ነው።
 
ኢትዮጵያ ደግሞ፥ መስመር ያልተዘረጋበት ሳይቆጠር፣ መስመር በተዘረጋባቸው አካባቢዎች መብራት ብርቅ ነው። መሀል አዲስ አበባ ዛሬም መብራት ሲመጣ በደስታ ይጮኻል። እናቶች ምጣድ ጥደው መብራት እየሄደባቸው፥ ሊጥ እየተበላሸባቸው፣ ጀሶ እና ሳጋቱራ ድብልቅ እንጀራ ሸምተው ቤተሰባቸውን እንዲመግቡ ተገደዋል።
 
ፋብሪካዎች እንደሚገባቸው አያመርቱም። (ያው አንዱ ቤተዘመድ እንዲከብር ያመጣው ጀነሬተር ተቸብችቦለት በሱ መጨናበስ አለ።) መብራት ባለመኖሩ ምክንያት ሥራ ፈትተው የሚቸገሩ ሰራተኞች አሉ። በጨለማ እየወደቀ የሚሞተው፣ የወንጀል ሰለባ የሚሆነው ተቆጥሮም አያልቅ። የመብራት ችግር ጣጣዎች ተዘርዝረው የሚያልቁም አይደሉም።
የኢዜአን ሙሉ ዜና ከታች አንብቡት….

ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ 400 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለመሸጥ የሚያስችል ስምምነት ልታደርግ ነው

ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ 400 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለመሸጥ የሚያስችል ስምምነት ልታደርግ ነው

አዲስ አበባ ነሀሴ 20/2008 ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ 400 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለመሸጥ የሚያስችል ስምምነት ልታደርግ ነው።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር አዜብ አስናቀ ለኢዜአ እንደገለጹት ሁለቱ አገሮች የሽያጭ ስምምነቱን በሚቀጥሉት ሳምንታት ያከናውናሉ።

ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ የምታቀርበው የኤሌክትሪክ ሃይል በኬንያ በኩል የሚያልፍ በመሆኑ በኬንያና ታንዛንያ መካከል የሚደረግ ስምምነትም እንዳለ ገልጸዋል።

ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ገዝተው መጠቀም የጀመሩት ሱዳን፣ጁብቲና ኬንያም ተጨማሪ ኃይል መጠየቃቸውን ኢንጅነር አዜብ ተናግረዋል።

አገራቱ ከውድና አካባቢን ከሚጎዳ የሃይል አጠቃቀም ይልቅ ኢትዮጵያ የምታመርተውን ታዳሽ ኃይል ለመጠቀም ያላቸው ፍላጎት እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል።

በቀጣይ አረጋቱ የጠየቁትን የኃይል ፍላጎት ለማቅረብ ተጨማሪ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎችን ለመሥራት ጥናት እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል።

እንደ ኢንጂነር አዜብ ገለፃ 200 ሜጋ ዋት ኃይል ፍላጎት ላላት ኬንያ ኃይል ለመስጠት የመስመርና የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ፕሮጀክት ተፈርሞ ወደ ሥራ ተገብቷል።

ኢትዮጵያ ለጎረቤት አገራት እያቀረበች ያለችው የኤሌክትሪክ ኃይል የአገራቱን ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት በማጠናከርና የልማት ትስስሩን በማፋጠን ላይ ይገኛል።

ግንባታው በቅርቡ የተጠናቀቀውና 1 ሺህ 870 ሜጋ ዋት ሃይል የማመንጨት አቅም ያለው ጊቤ ሦስት ሃይል ማመንጫ አሁን ላይ 900 ሜጋ ዋት እያመነጨ ነው።

በአሁኑ ወቅት ጊቤ ሦስትን ጨምሮ በአገሪቱ ያሉት ግድቦች የሚያመነጩትን አቅም ለመጠቀም የሚያስችል የሃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ጣቢያዎችን አቅም የማሳደግና አዲስ የመዘርጋት ሥራ በመከናወን ላይ ይገኛል።

ታላቁን የህዳሴ ግድብ ጨምሮ በግንባታ ላይ ያሉ ሌሎች ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ኢትዮጵያ ለሌሎች አገራት የምታቀርበው ኃይል እንደሚጨምር ይጠበቃል።

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀንድ ባሻገር ሩዋንዳና ብሩንዲ ለመሳሰሉ በጣም ውድና ታዳሽ ያልሆነ ኃይል ለሚጠቀሙ አገራት እንዲሁም ለሰሜን አፍሪካ፣መካከለኛው ምስራቅና አውሮፓ የማቅረቡ ዕቅድ አላት።

ታንዛንያ ከጅቡቲ፣ሱዳንና ኬንያ በመቀጠል ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የምታገኝ አራተኛዋ አገር ትሆናለች።

 ከዚህ በላይ አደገኛ ቦዘኔነት፣ ከዚህ በላይ ሽብር ከወዴት ይገኛል!?
 

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s