ፈርኦናዊነት

Hailemariam-Desalegnሰው ከመጽሐፍ ቢቀር ከእድሜው፣ ከእድሜው ቢቀር ከወዳጆቹ/ጎረቤቶቹ፣ ከነሱ ቢቀር አለትን ወደ አፈር በሚለውጠው ጊዜ፣ ከእርሱም ቢቀር ጨለማና ብርሃን ከሚፈራረቁበት የጠፈጥሮ ዑደት… እንዴት አይማርም?
 
በእኔ እምነት ይሄ ስርዓት እንኳን አሁንና ድሮም ያልፈረሰ፣ በከባድ ችግር ውስጥ እንኳን ገብቶ የማይፈርስ ስርዓት ነው። ስለዚህ በአለት ላይ የተመሰረተ ስርዓት አለን ብሎ ማመን ጠቃሚ ይሆናል። ….በዚህ ሂደት ውስጥ የተሳተፉ አካላትን ያለምህረት ህግ የማስከበር ስራችንን ማከናወን የሚገባን ይሆናል። መንግስት የህግ የበላይነትን ለማስከበር ሁሉንም አቅሙን ይጠቀማል። በእኔ በኩል ይህ የህግ የበላይነት እንዲከበር ለማድረግ ሁሉም የጸጥታ አካሎቻችን ህግ የበላይነትን እንዲያስከብሩ አዝዣለሁ።
ብሏል (ጠ/ሚ?) ኃይለማርያም ደሳለኝ
እንግዲህ ትዕዛዝ ማንበብ ነበርና ስልጣኑ’አለሁ’ ለማለት ጊዜ ተራው ደርሶት መሆኑ ነው ሕዝብ ለመፍጀት ትዕዛዝ ያስተላለፈው፡፡ ይሄ መቼም የሚረሳ ጉዳይ አይደለም!
 
ቃል በቃል ገልብጬው ደጋግሜ አነበብኩት። ደጋግሜ ነፈርኩኝ። የሰው ልጅ አእምሮ እንዴት በዚህ ደረጃ ሊደነዝዝ ይችላል? መቼስ ያደገ አገር ሰዎች ብንሆን እንዲህ ያለውን ሰው ሰብስበው ጥናት መከናወኑ አይቀርም ነበር።
 
“ፀጉራም ውሻ አለ ሲሉት ይሞታል” ነበር ተረቱ። “ፀጉራም ውሻ ሞቶም ሲታይ ጣረ ሞቱ ‘አለሁ’ ይላል” እንበለው ይሆን?!
.
.
ሰውዬው በሀይማኖተኛ ማሊያም እንደሚጫወት ትዝ ቢለን፥ ከመጽሐፍ ቅዱስ የፈርኦንን ታሪክ እናስታውሳለን….
 
“እግዚአብሔር እንደ ተናገረ፥ የፈርዖን ልብ ጸና፥ አልሰማቸውምም። እግዚአብሔርም ሙሴን አለው፦ የፈርዖን ልብ ደነደነ፥ ሕዝቡንም ለመልቀቅ እንቢ አለ።” (ኦሪት ዘጸአት 7፥ 13-14) “ግብፃውያንም፥ የፈርዖን ፈረሶችና ሰረገሎች ፈረሰኞቹም ሁሉ፥ እያሳደዱ በኋላቸው ወደ ባሕር መካከል ገቡ።” (ኦሪት ዘጸአት 14፥23)
 
“የሰው ልጅ ሆይ፥ ስለ ግብጽ ንጉሥ ስለ ፈርዖን ሙሾ አሙሽ፥ እንዲህም በለው። የአሕዛብን አንበሳ መስለህ ነበር፥ ነገር ግን እንደ ባሕር ዘንዶ ሆነሃል በወንዞችህም ወጥተሃል፥ ወኃውንም በእግርህ አደፍርሰሃል፥ ወንዞችህንም አሳድፈሃል።” (ትንቢተ ሕዝቅኤል 32፥2
 
“የመለስ መንፈስ ከኃይለማርያም ላይ ልቀቅ!” የምንልበት ጊዜ አልፏል። አሁን መንፈሱ ሙሉ ለሙሉ እንደተዋሃደው እያየን ነው። …እንግዲህ ሙሾ እያሞሸን ፍትህ ሲፈጸም የምናይበት ቀን ይመጣል! የሰው ልጅ ደም እንደው በከንቱ ፈሶ አይቀርም!
 
“ፈርዖንንና ሠራዊቱን በኤርትራ ባሕር የጣለ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና!” (መዝሙረ ዳዊት 136፥15)
 

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s