ሲደፈርስ!

ትግሉ መስመር እስኪይዝ ድረስ፥ እንኳን በኢትዮጵያ አንድነት ከሚያምኑ ኦሮሞዎች ጋር መስማማት ቀርቶ፥ የአማራ እና የኦሮሞ ዛፍነትና የስሮቻቸው ተጨባባጭነትም ይቀነቀናል። እስከዚያ፥ ተመልካች (audience) እየለዩ፥ ዓላማን ለመሸፋፈን እና ወቅታዊ ተቀባይነትን ለማግኘት፥ በየቋንቋው የተለያየ ነገር ያስተላልፋሉ። ስጋቱን ለመግለጽ የሚሞክር ቢኖር፥ በ“ትግል አታዳክም” ታፔላ ሊሸማቀቅ ይዳከራል። ትግሉ መስመሩ ተጠናክሮ ዳር ሊይዝ አጥቢያው ሲመስል ደግሞ፥ “አገር ይፍረስ! እንክትክቱ ይውጣ!” ይባላል።
 
ይገርመኛል! ፊደል መቁጠር ለዚህ ለዚህ ካልጠቀመ ለምን ሊጠቅም ነው? በተለይ በባዕድ አገር ላይ፥ “ከየት ነህ? ማን ነህ? ምን ቋንቋ ትናገራለህ? ለምን መጣህ?” ሳይባል፣ ተመቻችቶለት እንደልቡ እየኖረ እና እንደ ኅብረተሰቡ አካል ተመሳስሎ እየተማረ፣ በሞያው እያገለገለ፣ መብቱን አስከብሮ ሸጦ ለውጦ እየተዳደረ፣ ቢሻው ሀብት ንብረት እያፈራ እና ቋሚ እሴት እያጠራቀመ፥ እንዴት ለገዛ ወገኑ እልቂት መፈራረስን ይመኛል? በእንግድነት በተድላ ከሚኖርበት ቦታ እንኳን እንዴት ይህንን ትምህርት አልቀሰመም? እንዴት በመከራ ውስጥ ሆኖ ነጻነቱን ሲፈልግ፥ ባልጠገበ አንጀቱ በአምባገነን ስርዓት ወድቆ የቀረ ወገኑ ደም ላይ ይሳለቃል?
 
ይኽስ ማንን ይጠቅማል? ሰድቦ ለሰዳቢ አሳልፎ ለመስጠት ካልሆነ፥ ማንን ወደፊት ያራምዳል? እስከመቼስ በአንድነት እና በትብብር አብሮ የሚኖረው ሕዝብ፣ በሆዳም ‘አዋቂ’ ነን ባይ ፖለቲከኞች “አይ አብረህ መኖር አትችልም” ይባልለታል? ለእነሱ አገር በማፍረስ ዋጋም ቢሆን የሚገኝ የስልጣን ጥማት ማርኪያነት ለምን ይናፈቃል? ትናንት የመጡትስ ከዚህ መች ተለይተው ጀመሩት? ደግሞ፥ “ይሁን” ቢባልና ቢሳካስ በሰላም መኖር ይቻል ይመስላቸዋል? ወይስ በቃ አገሪቱን ተቃርጠው በየክልሉ ተመሳፍነው ሊያስገብሩ ነው?
 
እንዲህ ዓይነቱ ጨዋታ፥ የሴረኞችን ህልም ከማሳካት ይልቅ፥ ሙሉ አገሩ ስለአንድነቱ በጋራ እንዲቆም እንደተላለፈ ጥሪ የሚቆጠር ነው። አገራችን በጨካኝ ስርዓት እጅ ባለችበት በዚህ ሰዓት፥ ‘አገር አፍራሽ ሆነን፣ ልንበትንህ መጥተናል። እኛ መሲህ ነን’ ዓይነት ነጋሪት ብትጎስሙበትና ከያዘው ትግል ልታጓትቱት ብትጥሩ፥ አይምራችሁ! የነጭ ስልጣኔ፣ ገንዘብና የተሻለ ኑሮ ሳያጓጓቸው በባዶ እግር እና በጨበጣ ውጊያ ጣሊያንን እንኳን ገርፎ የመለሰ ሕዝብ አገር ሰዎች ነንና መቼም አይሳካላችሁም!
 
መተዋወቅ ያስፈልጋል። ስለማታውቁት፣ ወይም ድሮ አውቃችሁት ስለረሳችሁት ሕዝብ ነው የምትደሰኩሩት። “ዶሮ ብታልም ጥሬዋን” እንዲሉ፥ መከራ የፈነቀለውን እና በጋራ የቆመውን ሕዝብ “የኔ ጦር ነው…የኔ” ትባባሉበታላችሁ። ቢቆስል፥ ‘የውሻ ቁስል ያድርግልህ’ ያላላችሁትን፣ ቢሞትበት፥ የቤተሰቡን ትኩስ አስከሬን ፎቶ በየገጹ ከመቀባበል ያላላፈ፥ ጠንከር ያለ “ነፍስ ይማር” እንኳን ያላላችሁለትን፥ ደሙን ገብሮ ነጻነቱን ለመቀዳጀት ደፋ ቀና ሲል… ‘እኛ ነበርን እግዚአብሔሮችህ፣ ከኋላህ ቆመን በለው በለው ስንልህ የነበርን። አሁን ድል አገናኝቶን የባንዲራህን ጨርቅ አስቀድደን፣ ልንሰቅልልህና ልናሸጋግርህ መጥተናል’ ብትሉት አይሰማችሁም። ኢህአዴግም በብዙ ነገር ከፋፍሎ፣ በትንሽ ትንሹ ጠርንፎ፣ በሀውልትና በፕሮፖጋንዳ፣ ‘በታትኜ ያዝኩት’ ያለው ሕዝብ፥ አንድ ሆኖ እያስደነበረው ነው።
 
አሰቃቂው የኢሬቻ እልቂት ሳይቀር እንኳን፥ እንደጥሩ ትግል ማቀጣጠያ ቤንዚንነት ያስደሰታችሁና፣ እንደ ጥብስ ወሬ ያነቃቃችሁ፥ “የአገር መፍረስ ህልመኞች” እንዳላችሁ ልባችሁ የሚያውቅ ታውቁታላችሁ። ቱኒዚያ ቦአዚዝ ራሱን ቢለኩስ፥ ቤንዚን ሆኖ የነጻነት መንገድ እንደጠረገላቸው፣ ለግብጽ አብዮትም የካሊድ ሰይድ ግፈኛ አገዳደል እርሾ ሆኖ እንዳሰባሰባቸው፥ ሰው በሞተ ቁጥር ህልማችሁን የማሳካት ሴራችሁ ከግብ እንደተቃረበ በመቁጠር ብቻ… በመሰባሰብ ፈንታ፣ ‘የድል ዋዜማ ላይ ነንና ብቻችንን እንቁም’ በሚል ብልጣብልጥነት ስንቱን ለማግለል እንደጣራችሁም፣ ስንቴ በጠላት እንዳሳለቃችሁብን የምታውቁ ታውቁታላችሁ። ኦሮሞ ያልሆነ ሰው የኦሮሞ ፖለቲካ ላይ ሀሳብ ቢሰጥ፥ በ’oromophobia’ ፈርጃችሁት፣ ፍርሀትን ለመትከል የለፋችሁም ታውቁታላችሁ።
 
“እንለይህ” የምትሉት ወገን፥ በጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ እንኳን አንድ ቦታ የተከማቸ፣ ባህሉንም ያልተወራረሰ አይደለም። እንለይህ የምትሉት ወገን፥ እንጀራ ተበዳድሮ እና ሚጥሚጣ ተዋውሶ፣ ለቡና እየተጠራራ፣ ልጁን እርስ በርስ እየተቀጣጣ፣ ቤቱን ቁልፍ አልባ ትቶት “መጣሁ” ተባብሎ የኖረ ነው። ጡት ሳይቀር ተጋርቶ ያደገው ሕጻን ብዙ ነው። በከተሞች ብልጭ ድርግም ባይ መብራቶች የተጋረደ ብዙ ያልታየ ሕዝብ አለ። በአካባቢ መቀየር እንኳን የኑሮ ቀውስ የሚገጥመው ሕዝብ ነው።
 
“ጠላቶችህ ናቸው” ብላችሁ ስለወዳጆቹ ክፉ ለመንገር የምትደክሙለት ሕዝብ ያን ያህልም ክፉና ደግ የማይለይ እንዳልሆነ እንኳን አትገነዘቡም። ንቃችሁት ተነስታችሁ ነው እናስከብርህ የምትሉት። ከዚህ በላይ ‘እየታገልኩልህ ነው’ የሚሉትን አለማወቅ የለም!
 
የወገኖቻችን ደም በከንቱ ፈሶ አይቀርም!
 
ይጮሃል! ሁሌም ይጮኻል! ከጩኸቶቹ ሁሉም የጎላና የከበደ የሚሆነው፥ ‘ምሁራን’ ተሰብስበው ደሙን ሊያቃልሉበትና፣ ለጠላቶቹ መስዋዕት ሊገብሩበት እንደሆነ ያወቀ ጊዜ ሳይሆን አይቀርም።
 
የደፈረሰው ጠርቶ፣ የተከፈለው መስዋዕት እንደሚያጠባብቀንና ልቦቻችንን አክሞ በጋራ እንደሚያኖረን፣ አገሪቱንም ለሰው ልጆች ሁሉ የሚመች ስርዓት የሰፈነባት እንደሚያደርግ አልማለሁ!
 
ከዛሬ ነገ ይሻላል!
 
#Ethiopia

It will not be far…

The internet blackout and blockage of social networks in #Ethiopia is a blessing in disguise; and another big strategic mistake of the brutal government. It is a significant add-on to the mass protests, and tells the World once more again about the kind of government we have. As well, it has a good effect of letting the people focus on the effective and less costly interventions.
 
Our cyber activities were, somehow, keeping us aback from proper understanding of the extent that our freedom of speech is banned, and our potentials to get rid of it. Innermost, ‘being an active user of the internet’ might have created a humdrum feeling, and vapid feelings of ‘freedom fighter’ with every status update made and with every conversation held, while it hasn’t even kept us an inch closer to what is required and to our capacity.
 
If people are forced to logout facebook and other social networks, what the hell the tyrants are expecting them to do? They will login to the real world, and get organised in their communities to the fullest, so as to let brutality logout of the land for once and for all. The brutal regime is working hard to let that materialize, and organizing the people for a good cause of getting freedom.
 
Change is inevitable!, as “change will not come if we wait for some other person or some other time. We are the ones we have been waiting for. We are the change that we seek.” (Barack Obama) …and here we’re awake!, and we’ll stay united!
 
We have also learned that violence is a magic that multiplies defiant souls. When problems become devastating, solutions are promising. Now, the country has concerned and determined citizens more than ever. And speaking up for those who can’t is being a passion and it is being less confused with hard politics, and soon freedom will be a fashion for us to cherish and for our children to live in.
 
I am too positive that fighting for human rights and standing up with morale, in all fields, will be ordinary, not a bravery act for few to practice it and many to get astonished about.
 
It will not be far that they will pay the price; and amid, we will thank them for they are being on the power side of the powerless.

ለቁም ነገር ስንጠራ

ማፈን መፍትሄ ኾኖ ቢያውቅ ኖሮ እንዲህ ባልደነበሩ ነበር። “ፀጉራም ውሻ አለ ሲሉት ይሞታል”ን በልባቸውም ቢሆን ለራሳቸው ባልተረቱ ነበር። ይኸው አዲስ አበባም ላይ የስልክ እና የሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎቾን እንዳቋረጡ ነው።
 
ይኼ ማለት፥ ምንም እንኳን በየልሳናቶቻቸው እየቀረቡ፣ የማኅበራዊ ሚዲያዎችን እና ተጠቃሚዎቻቸውን በማውገዝ እና፣ በማንቋሸሽ ቢጠመዱም፥ የሚዲያዎቹን ሚና የሚያጣጥሉት እንዳልሆነ እየመሰከሩ ነው። የሚሸበሩት በመግባባታችን መሆኑን እየተናገሩ ነው። ቆዩ! ፍቅረኛቸው ብንሆን ኖሮማ “ብቻዬን ላገኝሽ ብጓጓ፣ ኢንተርኔት እስካቋርጥ… ስልኬን እስካዳፍን ድረስ ራድኩልሽ” ብለው ግጥም ሳይጽፉልንም አይቀሩ ነበር።
 
“ሥራ ያጣ ቄስ ቆብ ቀዶ ይሰፋል” ሲባል ዝም ብሎ ነገር ማሳመሪያ ተረት እንደኾነ አድርገው ቆጥረውት ይሆናል። የረባ ነገር አስበው አያውቁምና አልፈርድባቸውም!
 
የሕዝብን ገንዘብና የአገርን ሀብት እየበዘበዙ በሙስና ሲጨማለቁ፥ ‘ኢኮኖሚውን ምን ቀይሰን እናሳድገው? ምን የሥራ መስክ እንፍጠርለት? እንዴት እናሳትፈው፣ በገዛ አገሩ እንዲሰማው ያደረግነውን የእንግዳነት ስሜቱን በምን እንቅረፍለት?’ ብለው ተጨንቀው የማያውቁለት ስንትና ስንት ተመርቆ ቁጭ ያለ ለጋ ወጣት፣ ሥራ ፈልጎ ቢያመለክት ያሸበረቀ የባለሞያ ሲቪው እንዲታይለት ዘመድ ወይም የፖለቲካ ተሳትፎ እያስፈለገው፥ ተስፋ ይኾናል ሲባል ከኅሊናው ጋር እየተሟገተ ተስፋ ቆርጦ ቁጭ ያለ ወጣት፣ ከቤተሰብ በሚያገኘው ድጎማም ቢሆን ኢንተርኔት ላይ ቢጣድ፥ በሥራ ተጠምዷልና ስጋት ይቀንሳል።
 
ሌላም፥ ተጠቃሚውም ሰው በሚጽፋቸው ስታተስ አፕዴቶች እና በሚሰጣቸው አስተያየቶች የተነሳ “እየታገልኩ ነው” ብሎ ማሰቡና ራሱን ማጽናናቱ አይቀርም። ኢንተርኔቱ ሲቋረጥ ግን፥ በየፌስቡኩ መገናኘት የለመደ ሰው፣ መንደር የመቀየር ያኽል face to face መገናኘትን ማሰቡ አይቀርም። ይኼ ትንበያ አያሻውም። የኖርንበት ነው።
 
ቤት ውስጥ ሆነን፣ ኢንተርኔት ሲቋረጥ ከፌስቡክ ወጥተን ቤተሰቦቻችን ጨዋታ መሀል ገብተን እናውቃለን። ለጨዋታም ቢሆን ቤተሰቦቻችን ለቁም ነገር ሊያገኙን ሲፈልጉ የኢንተርኔት አፓራተሶቻችንን ደብቀውብን ያውቃሉ። ኔትዎርክ ሲቋረጥ ለሻይ ተሰብስበን ስልኮቻችንን መነካካቱን ትተን እርስበርስ ማውራት ጀምረናል። ያለንበትን የኑሮ ዓይነት እና አካባቢውን ቃኝተን “ምን እናበርክት?” ብለናል። ደጃፍ ላይ እንኳን “ችግኝ እንትከል” ተባብሎ የሚስተባበረው ከኢንተርኔት ላይ ወጥተው ሰፈር ውስጥ ሲገኙ ነው።
 
አንክድም፥ ዕውቀት ገብይተንበታልና የኢንተርኔት ሱሰኞች ኾነናል! ብድግ ብለው፣ ያላስታመሙት ሱሰኛ ሱስ ላይ በር መዝጋት ምን ዓይነት ተጽህኖ እንደሚፈጥር፥ የጭቆና እና የገዳይነት ሱሰኞች ናችሁና አይጠፋችሁም። አሁን ምን ጎድሎበትና ምን አግኝቶ ፌስቡክ ውስጥ ሲሸሸግ ሱሰኛ እንደሆነ ያውቃል። ሳይወድ በግዱም የጎደለበትን ይፈልጋል። ምስጋና ግንኙነት ያቋረጠ መስሎት፣ በአካል የመራራቅ ምሽጉን እየሰበረ ላለው አምባገነኑ መንግስት!
 
አሁን መንግስት ወጣቱን ለቁም ነገር ሳይፈልገው አልቀረም ኢንተርኔቶችን ዘግቷል። እንጂማ ሰላሙን ቢፈልግ፣ እንኳን ኢንተርኔት ሊያጠፋ፣ ዜንጦ ስልኮች (smart phones) የሌላቸውን ኹሉ ከሲም ካርድ እና ነጻ የአየር ሰዓት ጋር እያስታጠቀ በየማኅበራዊ ድረ ገጾች እንዲመሽግ ያደርገው ነበር። 🙂

ግድቡማ

እንገንባ ሲሉን ግድቡን ነው ብዬ
ቦንድ ግዙ ሲሉን ለልማት ነው ብዬ፣
ለካስ ለምሽግ ነው፥ ለሚሸጎጡበት…
ሲያጥለቀልቃቸው ጎርፍ ሆኖ ዕንባዬ!
 
ይኸው ደግሞ ወደንም ኾነ ተገደን፣ ላባችንን ጠብ አድርገን እያስገነባን ባለው “የአባይ ግድብ” ማስፈራራት ጀምረዋል። እንደምናየው እያስፈራሩን ያሉትም በራሳችን ንብረት ነው። የሕዝብ ብሶት ጦር ኾኖ ሲንቀለቀልባቸው፣ አባይን ተጋሸን (ጋሻ ሁነን) እያሉት ነው።
 
አሁን ነው “ወንድምና ወጥ ማስፈራሪያ ነው።” ብለው ሚሸልሉት። ግን እንጀራው ሲሻግት ወጡ በስትራው አይመጠጥ! እንጀራው ሲደርቅ ወጥ ትሪ አያስፈራራ! ደግሞ ተገንብቶ ኃይል ሲያመነጭስ ለእኛ ይትረፍ አይትረፍስ በምን እናውቃለን? እኛን በጨለማ “የሽንብራው ጠርጥር”ን እያስዘፈኑ ለሌሎች አፍሪካ አገራት መብራት እየቸበቸቡትም አይደል?
 
እኛ ቁርበት ላይ ስንቆራፈድ በስንትና ስንት ሚሊዮን ብር ቪላ አንጣለውም አይደል? ለቀድሞው ፕሬዝዳንት አቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ ሳይቀር በወር 450 ሺህ ብር ቤት ኪራይ እየከፈሉ፣ ሰውዬውን ገዳም ገብተው ንስሀ እንዳይቀበሉ (እሳቸውን እንጥቀም ብለው ይሁን አከራዩን፥ እነሱ ያውቃሉ።) የከለከሏቸው በሕዝብ ገንዘብ አይደል?
 
ከዘፍጥረት አንስቶ፣ ገነትን ያጠጣ የነበረ፣ ከኤደን የፈለቀው የጊዮን ወንዝ እንደው ከአምባገነኖች ጋር ሕብረት አይኖረውም። ጩኸታችንንም ይዞት ይሄዳል። የምናምነው ያየናል። እንኳን ባሮቹን ሊፈጅ የመጣ መሰሪ ስርዓት፥ ይኹን ሲባል የኢያሪኮ ቅጥርም ከመውደቅ አልዳነም። ፈርኦን ከነጭፍሮቹም አልተረፉም። መልከ ጼዴቃዊ ሹመት ለግፈኞች ቃል አልተገባም።
 
የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ሁሉም ሂሳቡን ያወራርድ ዘንድ ግድ ነው!

ኢሬቻ

ed0665b9a76b426480aa73c26a057bc8_18አበባ ቀጥፌ፣ ምስጋና ሸክፌ፣
“ዋቃ ገለቶሚ” ልልህ አሰፍስፌ
መጥቼ ነበረ፥ ሰንበትን ቆጥሬ፣
ለከርሞው ልማጸን፥ ውዳሴ ሰፍሬ
ግጥሜን ደርድሬ፣ እልልታ ቀምሬ
ሀሴትን ቋጥሬ፥ የከንፈሬን ፍሬ፤
እኔን የቆሉበት ጢስ ሰማይ ላይ ወጥቶ፥
አጨናብሶህ መሰል፥ እንዳታይ አጥርቶ፣
ዘንድሮስ አልሞላ ቀጠሮ ታጎለ፣
ሳንተያይ ቀረ
ስጋ ዳገት ሰራ፣ ካፈር ተከመረ፤
ዋቃዮ የታለህ?
ብጣራም አልመጣህ ጭራሽ አትሰማ
በደም ተነከረ ያቀፍኩት ቀጤማ፤
ጽልመት ተነባብሮ ድቅድቅ ባለ ቁጥር፥
“ጽጌ ሊጠባ ነው፣ ሊነጋ ነው” ብዬ መጓጓቴም ከሳ፤
በነጎድጓድ ብዛት ሰማይ ሲተራመስ፥
ረግቶ ማያውቀው ሀይቅ፥ ክፉኛ ሲታመስ፥
“ምህረት ሊዘንብ ነው፣ ጥሩ ልጠጣ ነው”
ብዬ መጠበቄም፥ ጫነብኝ አበሳ፤
ኤሳ ጂራ ዋቃ?
ጋረደኝ ጨለማ፣ ደድሮ ተነሳ
የልቤ ክረምቱ በጣ’ይ ተከመረ፥
ብሶት እንባ መስሎ ካይኔ ተከተረ፤
ደሙን ተራምጄ ደም አደናቀፈኝ
እንባውን አልፌ እንባ ጠላለፈኝ፣
ዋይታውን ብዘለው ዋይታ ተቀበለኝ፥
ብሄድ ወደ ግራ፥ ብታጠፍ ወደቀኝ
ለቅሶና መከራ፣ ታጅቦ ጠበቀኝ፣
እስረኛው ጉያዬም በእሳት ተቃጠለ፥
በግፈኛው ሚዛን ሰውነት ቀለለ፤
ንገረኝ ጌታ ሆይ…
ስንት ተስፋ ይንጠፍ?
ስንት ጀምበር ይለፍ?
ስንት አበባ ይርገፍ?
ስንት ሰው ይሰዋ፣
እንዴት ይሙላ ጽዋ?
አይጥ በጠገበ፥ ስንት ይገረፍ ዳዋ?
ስንት ዳስ ይደርደር፣
ስንት ገጽ ይቧጨር?
ስንት ደረት ይፍረስ?
ስንት አጥንት ይከስከስ?
ከገጠር ከተማ፣ ስንሞት፣ ስንደማ፥
እንድታየን አንተ፣ ስንጮኽ እንድትሰማ?!
/ዮሐንስ ሞላ/

 

መርጠውና ለይተው፣ በእውቀትና በጥናት ላይ ተመርኩዘው ያደረጉት ነገር አይደለም። ልክ አፈጣጠራችንና በስጋ አዘማመዳችን እንደ እድል እንደሆነ፥ ሞታችንንም እንደ ዕድል ነው ያደረጉት። ካልደገፍናቸው፥ ኑሯችን እንደነፍሰጡር ሴት፥ ደርሶ እስኪታይ ድረስ መጪው የማይታወቅ ነው።
 
ስላልገደሉን ነው እንጂ ሁላችንም ላይ ተኩሰዋል። ስላልታሰርንላቸው ነው እንጂ ሁላችንም ላይ ሰንሰለታቸውን እያንሿሹ ሸልለውብናል። ስላልጣሉን ነው እንጂ ሁላችንንም ገፍትረዋል። ቅሬታን መግለጽና ይሻላል ያሉትን ሀሳብ መናገር ነውር እስኪመስል ድረስ በፍርሀት እና በሽብር ጠፍንገውናል። መፈጠራችንን እስክንጠላ ድረስ እርቃናችንን ለማስቀረት ደክመዋል።
 
እኛም አለን እስካሁን ከለቅሶ ለቅሶ እየዘለልን። ጨረስናቸው ሲሉን እንደ ምድር አሸዋ በዝተን እንኖራለን ገና!
 
እኔ ብሆን ኖሮስ?? እናቴ ብትሆን ኖሮስ?? ልጄ ቢሆን ኖሮስ?? ወንድሜ ቢሆን ኖሮስ?? እህቴ ብትሆን ኖሮስ?? ፍቅረኛዬ ብትሆን ኖሮስ?? የልብ ወዳጄ ቢሆን ኖሮስ?
 
“ማነሽ ባለተራ”
ጥርስ ውስጥ የገባሽ?
 
አናውቅም! ማንም አያውቅም!
 
እነሱም መግደልና ኡከት መፍጠር ሞያቸው ስላደረጉት እንጂ፥ ነገም ተቃዋሚውን መግደላቸውን እንጂ ማንን መግደላቸውን አያውቁም። ከገደሉ በኋላ ደግሞ ቁጥር መሸቀብና መቀርቀቡን ያውቃሉ። መዋሸቱን ያውቃሉ። እንጂ አገዳደሉ እንደገበያው ነው። ቤቱ ክፍት እንደተገኘበት ነው የጅብ አገባቡ። ጎረቤቱ እንደናቀው ነው የአጥር አነቃነቁ።
 
ሁላችንም በጋራ መነጋገር ካልጀመርን፣ ማውራት እና መደማመጥን ካላበረታን፣ እርስበርስ ካልተጠባበቅን ይጨርሱናል። በአንድነት ካልቆምን ለቅሷችን አያባራም፣ ድንኳናችንም አይፈርስም።
 
እግዚአብሔር ከተጎዱት ጋር ይቁም! በቃችሁ ይበለን!
They have killed many, they have knocked on many houses. They have tried to close many doors and mouths, they have helped for many more to be opened. They distracted many alert and concerned citizens, they have alarmed on many dormant, ignorant, and natural ones. They have hammered many heads, they have awaken many neurones. They have given the earth a blood bath, they have called many to give blood for the nation to get a bath towards purity.
They raped a nation brutally, they have impregnated it breaking strong eggs with their inhuman sperms. They have killed, they have given birth to many. They didn’t know that throwing a seed means promising for it get rooted deep, and many of its kinds to come in fresh forms; as well, cutting the trunk is giving new branches a time of vegetating to trunks.
 
Through the blurs of our tears, we see many are joining in protesting the brutality, speaking up for those who can’t, and standing in solidarity with the victims. Now, concern will not be confused with politics, nor political awareness and activism will not be taken as a very wrong of the doers. Though a different kind of pain is inflicted in our hearts, eventually, knowing we all are mortals, we all know that it is a blessing in disguise.
They never loved us. They never loved to see us walking peacefully, to see us smiling, loving each one another, or having any undistracted day. Our peace is their mourn. Our holidays have been their peak times of terrifying us; our concerns and assemblies, their most terror. They were hate itself while we were celebrating Epiphany, Eid, Irreecha…even on the very secular great Ethiopian runs, they have been pains.
Demonstrations against violence of Saudi Arabia and Isis were among their public moments to show their sheer hatred for us. They have been distracting us with their guns, shackles, year gases, and physical and emotional tortures. Whether they saw us taking initiative to better community service plans, or they see us partake voluntarily, they never failed to see us with scorn. They never failed to prove us right that they have been consistent killers.
 
What has happened today is beyond our capacity to hold the pain, beyond what one can imagine, something that leaves one in shock even to properly cry about. I’m just acting weird; I can’t sit, nor I can stand properly…I can’t walk, nor loiter firm. I imagine how all you are feeling; it can’t be different, as our sufferings have been the same. They can’t hide it that it is a smart phone era that thousands have reported it with evidence. They couldn’t think, as we all have records in our minds. It is not about politics, but about humanity. It is not protesting, but speaking up against the devil itself.
 
But how many days shall we wait for?, how many nights to see us not being tortured to death? Is it the plan God? The beginning or the end? Revel, please. Egzio!
My heartfelt condolences to the innocent victims.
 
Death to bloody killers!