የሁለት ፕሮፌሰሮች ወግ…

 “ከቤተሰቤ መካከል አማርኛ የምችል እኔ ብቻ ነኝ።mqdefault
ሌሎች 13 ወንድምና እህቶቼ አማርኛን እንዳይሰሙም
እንዳይናገሩም አድርገን በጥሩ ሁኔታ አሳድገናቸዋል።
አሁን ያለዉ የቁቤ ትዉልድም ከሞላ ጎደል አማርኛን
የማይናገር የማይሰማ ጀግና ትዉልድ ሆኗል።”

~ ፕ/ር ህዝቅኤል ጋቢሳ (በOMN)

merera-gudina100

“ቋንቋን በአግባቡ ያለመጠቀም የኦሮሞ ሕዝብ ተገቢ የመብት ጥያቄዎችን ለሌሎች እንዳያስረዳ እንቅፋት ከሆኑበት ነገሮች አንዱ ይመስለኛል፡፡ በ1983ቱ የሽግግር ጉባዔ ላይ እነ ኦቦ ሌንጮ ለታ ለየት ለማት በአስተርጓሚ ለመናገር ሲሞክሩ፣ አቶ መለስ በመንዝአማርኛ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ሲፈልጥና ቆርጦ ሲቀጥል ነበር፡፡ ፓለቲካ ለሚያውቅና ለገባው ሰው፣ ኦሮሚፋ አንድ ቀን እንኳ በአደባባይ ይሰማልን የሚባል የአናሳ ቡድን ቋንቋ ሳይሆን ትልቁ የኢትዮጵያ ብሄር የሚናገረው ቋንቋ ነው፡፡ ሙዚየም ውስጥ ይቀርብኛል ተብሎ የሚሰጋለት ቋንቋ አይደለም፡፡ የቋንቋ ፖለቲካ የማይናቅ ባይሆንም፣ በተገቢው ጊዜና ቦታ ካልተጠቀሙ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ሊያመዝን ይችላል፡፡”

~ ፕ/ር መረራ ጉዲና – “የኢትዮጵያ ፓለቲካ ምስቅልቅል ጉዞና የሕይወቴ ትዝታዎች ከኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ እስከ ኢህአዲግ” ገፅ 225

ቋንቋ

መግባቢያ ነው። ክህሎት እንጂ እውቀት አይደለምና ባይችሉ አያሳፍርም። መቻሉም ቢያስደንቅና ቢጠቅም እንጂ፥ የተለየ ሆኖ የሚያስኮፍስ ነገር አይደለም። ሰው እንደዋለበትና እንደፈለገው ልክ የትኛውንም ቋንቋ ማወቅና በአግባቡ የመጠቀም ክህሎቱን ማሻሻል ይችላል። ብዙ ቋንቋ ባወቀ ቁጥር ግን የተሻለ መግባባት እና መፍትሄ ማምጣት ይችላል።

በተለይ፥ ቋንቋውን ሆነ ብሎ ላለመማር መጣርም ጉልበትና ጥረት ይጠይቃልና ራሱን የቻለ ድካም አለው። ማለዳ ማለዳ ተነስቶ፥ ልጆችን ስለጥላቻ መስበክ፣ እሱን ቋንቋ እንዳትናገሩ ብሎ መጨቆን፣ ጓደኞቻቸውን መምረጥ፣ ውሏቸው ላይ ጣልቃ መግባት… ሁሉ የመብት ጥሰቶች ሆነው ያስወቅሳሉ እንጂ፥ እንደጥሩ ገሪነት የሚያስደንቁ አይደሉም። ወላጅ/አሳዳጊ ከዚህ በላይ ሊበድልም አይችልም!

እኔ ኦሮሚኛ ለመማር ከምደክመው በላይ (አዲስ ቃል ብሰማ እና አፌ ውስጥ ቢገባ ለመጠቀም እደጋግመዋለሁ እንጂ ስለመርሳት አልጨነቅም) እነ ፕሮፌር እዝቅሔል ቤተሰብ ልጆቻቸው አማርኛ እንዳያውቁ የደከሙት ሲታሰብ ያስቆጫል። ልጆች ከሰው ጋር ተግባብተው እንዳይኖሩ መፍረድ ኅሊና ላለው ሰው ግፍ ነው።

በክልልስ እሺ፥ መንግስትም ለይስሙላ ፌደራሊዝሙ ሲል “በአፍ መፍቻ ቋንቋ አስተምራለሁ” ይላልና በዚያ ያልፋሉ። 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሲመጡ መግባባት ከባድ ይሆናል። ዩኒቨርስቲ ሲገቡም እንዲሁ ሆኖ ሰው ባያገል እንኳን ራስን ማሸሽም ይከሰታል። ሕብረተሰብ ካልተግባባ ደግሞ ግፈኞች ጥሩ ምሽግ ያገኛሉ።

ስለታሪክስ ቢሆን በአንድ ቋንቋ እና ወገን ብቻ የተነገረውን፣ እንደዶግማ ከመጋት፣ ብዙ ማስረጃዎች (resources) ያሉበትን ቋንቋ፥ “ላስተምር” ብሎ መጣር ቢቀር፣ “እንዳይማሩ” ብሎ መነሳት ክፋት እንጂ ሌላ ምን ምክንያት አለው?

በአሜሪካ

20160709_200649ፕሮፌሰሩ እዝቅሔል ገቢሳ፣ ካለክልሉ አስጠግታው፣ ቤት ንብረት አፍርቶ፣ “ሰዎችን ከክልላችን ውጡ” እያለ እንደልቡ እየተከፈተ በሚኖርባት እና በሚያስተምርባት አገረ አሜሪካ…

ሰሞኑን የሜሪላንድ የጤና መድኅን ዋስትና ማዕከል፣ ለደንበኞቹ የላከው ደብዳቤ ላይ ወደ 17 የሚጠጉ ቋንቋዎች (Bassa የሚባል ስሙን ሰምቼው የማላውቀው እና፣ ‘Khmer’ እና ‘Laotian’ የሚባሉ ቋንቋዎች፥ ፊደሎቻቸው እርስበርስ ተያይዘው ሸረሪት ቀለም ነክታ ወረቀቱ ላይ የሄደችበት መስለው የሚያስቁ ሳይቀሩ ተካተው) ተጠቅሞ ያስተላለፈውን መረጃ ተመልክቼ ነበር። ከቋንቋዎቹ ውስጥ፥ አማርኛ እና ኦሮሚኛም ተካተውበታል።

በአማርኛ የተጻፈው….

“ያለምንም ክፍያ በራስዎ ቋንቋ እገዛ የማግኘት መብት አለዎት። ስለማመልከቻዎ ወይም ከጤና ዋስትና ድርጅቱ ስለሚያገኙት ሽፋን ማንኛውም ጥያቄዎች ካሉዎት፣ ወይም ይህ ማሳወቂያ በግልፅ በተጠቀሰ ቀን ማድረግ ያለብዎ ነገር እንዳለ የሚያስገድድዎ ከሆነ፣ በተጠቀሰው የስልክ ቁጥር ለስትቴትዎ ወይም ለክልልዎ ደውለው ከአስተርጓሚ ጋር ይነጋገሩ።” ይላል።

20160813_193553አሜሪካ ውስጥ፣ ከቆሻሻ መጣያ ቅርጫቶች አንስቶ በተለያዩ ቦታዎች፥ የአማርኛንም ሆነ ሌሎች ቋንቋዎችን ተጠቅመው ለመግባባት ሲጥሩ ይታያል። በሂደቱ፥ የሚያስቁ አጠቃቀሞችም አይጠፉም።

ከገጠሙኝ መሀል፣ በ’ዋሽንግተን ኤቲካል ሶሳይቲ’ አዳራሽ መጸዳጃ ቤት ግድግዳ ላይ “Do not put paper towels in the toilets.” የሚለውን መልእክት በ5 የተለያዩ ቋንቋዎች ለማስተላለፍ ሙከራ ተደርጓል። በአማርኛ የተጻፈውን ስመለከተው፥ “ዶ ኖት ፑት ፓፐር ቶወልስ እን ቶእለፅ!” ይላል። 🙂

ስንት አለ ቶእለፅ ራስ አቦ!? …ሳይሾም የነገሰ፣ “እሟገትልሃለሁ” የሚለውን ኅብረተሰብ ሳያውቅ የሚንቧቸር የእንግዴ ልጅ!

Good news…

Habitamu-Ayalew.jpgThe long waiting and imploring have come to an end, finally! The cruels banned what shouldn’t be banned in the first place, – ‘traveling for better medication’, even traveling for leisure would have been up to the individual… now, they have ‘allowed’ and we’re happy that Habtamu Ayalew is safe in USA. This is an ever ugly drama: ‘they take our rights’, and when they give us back, ‘we celebrate’.

But if one can afford, why not even to the Mars, even to the Moon? What the hell should the government get to do with it? But this is how it is when ‘gun’ governs… it even would have been worse.

Hallelujah! And congrats for all who have been concerned. And all the best Habtish and family!

—-

Habtamu Ayalew, has beenformer spokesman of the opposition, Andenet (Unity), Party, and he was arrested on July 8, 2014 and charged with ‘terrorism for allegedly collaborating with the opposition Ginbot 7’, which the Ethiopian government has proclaimed as ‘a terrorist group’. Habtamu was detained at the notorious Maekelawi and Qilinto Prisons, where he was subjected to torture and other ill-treatment through denial of access to toilet facilities, ‘a situation that led to him to develop excruciatingly painful hemorrhoids’. He was banned from leaving the country because the prosecutor has appealed the ‘release from prison’ decision of the High Court. As known, his hemorrhoids were easily treatable, hadn’t it been left untreated to get worse to stage 3. 

 

 

የማንሳት ኃይል

እደጃፌ ወድቆ
ሳየው ኑሬ ኑሬ
ወዳጄ ሲያነሳው፣ ውድነቱን አውቆ
በንፍገት ደንብሬ፥
ልቤ ሊያብድ ተጨንቆ፣
ነፍሴ ሊበር ወልቆ፣ ስጋዬን አሳቅቆ።
እደጃፌ ወድቆ
“ለእግዜር” እንኳ ባልል፣
ለዐይኔ ተቆርቁሬ
ሳላነሳ ትቼው፣
ሲንደፋደፍ ከእግሬ
የቀረን ምስኪን ሰው
ስለነፍስ ያደረ ሳምራዊ ሲያነሳው፥
መጽደቁን ቆጥሬ፣
የደጉን ተጋድሎ፣ ባገር መወደሱን
በሀሳቤ ዘርዝሬ፣
በቁጭት ተቀጣሁ፣
ዋልኩኝ ተንጨርጭሬ
በክፋት ደንብሬ፣ በቅናት ታጥሬ።
* * *
ነገር ግን ይገርማል!
 
ወዳጅ ባየው ቅጽበት
ባነሳበት አፍታ፥
በተመኘው ጠዋት፣
ባጌጠበጥ ማታ፥
የጣሉት ይከብራል
ዋጋው ይጨምራል።
* * *
ጥፍጥናዬን ምጎ፣ መረቄን ጨርሶ
ከአውላላ ሜዳ ላይ የተፋኝ አንኳሶ፥
ስደክም የዘረረኝ፣ ስወድቅ የረገጠኝ
ስንከራተት ደጁ፣ ያልጣለልኝ ከእጁ
ያልነበርኩ ወዳጁ፥ ቆለለኝ ስነሳ
ካበኝ በየፈርጁ፣ ሰፈረልኝ ካሳ።
* * *
ለካስ ለመላ ነው የሚለው አገሩ፥
“የወደቀን አንሱ፣ የሞተን ቅበሩ”
ካለፈ እንዲማሩ፣ በወግ እንዲኖሩ
እጃት እንዲጥሩ፣ ዐይናት እንዲበሩ።
 
/ዮሐንስ ሞላ/