ኧረ ገንዘቤን ለቀቅ!

አንዳንዱ ግንድ ተሸክሞ “አባይ ማደሪያ የለው”ን ሲተርት ዕድሜውን ይፈጃል።
 
ገንዘቤ ባንዲራው ኮከብ ስለሌለበት አስቀምጣው ሄደች ብሎ፣ እየተመላለሱ “አገር ይያዝ” ማለት ምንድን ነው? (“ወረወረችው” ማለት አጓጉል ግነት ነው።)
 
ባለፈው “በ25 ዓመቱ ጎንደር ላይ ታየ” ብለን አልነበር እንዴ ከዳር ዳር ስንፍነከነከ የነበረው? የፖለቲካ ፓርቲ ሰልፍ ቢጠራ ወይ ሕዝባዊ ስብሰባ ቢደረግ፣ ስታዲየም ውስጥ ጨዋታ ሲኖር፣ አገር ውስጥ ኾኖ ኮከብ የሌለበትን የሚጠቀም አለ? 
መንግስትን አጥብቆ እንደሚጠላ እየገለጸ ሰልፍ እና ስብሰባ ሲኖር የሚገኘው እና፣ ለተቃዋሚ እና ለሚዲያ አካላት የ“አይዟችሁ” (emotional support) ድጋፍ ለማድረግ የሚሞክረው ምን ያህሉ ነው?
 
“የሰንደቅ ዓላማ ቀን” ይከበር ብሎ መንግስት አስገድዶ በየሱቁ እና በየቅያሱ ባንዲራ ሲያሰቅል፣ “ይኼ ኮከብ ስላለው አልሰቅልም” ያለ አለ?
ምን ያህል ሰውስ ኮከብ የሌለው ባንዲራ ቤቱ አለ? ቢኖረውስ እንደ አያት ውርስ ጌጥ፣ ከስንት አንዴ እያወጣ፣ መልኩን እያየ ያስቀምጠዋል እንጂ አደባባይ ላይ በሚደረጉ ፌስቲቫሎች ይዞት ይወጣል?
 
ለምንድን ነው እኛ ለማድረግ የምንፈራውን፣ ቤተሰቦቻችን እንዳያደርጉ የምንከላከለውን፣ ወይም ጊዜና ሁኔታ እንዲሁም ቦታ አመቻችተን ያደረግነውን ነገር ሌሎች እንዲያደርጉ የምንጠብቀው? 
 
የ90 ሚሊዮን ሕዝብ ጭንቀት ጀርባቸው ላይ ተሸክመው ሮጠው፣ አንገታችንን ቀና ለማድረግ ደፋ ቀና የሚሉ አትሌቶችን የፕሮፖጋንዳ ቅመም ማድረጉን ትተን፣ የፖለቲካ ሲስተሙን ማብጠልጠል፣ እርስበርስ መባላቱ ተትቶ በጋራ ስለመቆም መምከር የተሻለ ይሆናል።
ካለዚያ ግን በየዘርፉ ጠላት ከማበርከት የተሻለ ሚና አይኖረንም።
China Athletics Worlds
ብዙ ኑሪልን አቦሸማኒት ❤
 
 

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s