“Donkey Meat Up for Export, Slaughterhouse Opens” – Fortune

ሲለፋ የኖረው በሸክም በዱላ
የአህዮቹ ገላ
ቀረበ ተልኮ፣ በጀማው ሊበላ
ታጨ ለስል ቢላ።
* * *
ተርፏቸው ሳይሰጧት
“ማር አይጥማት” ሲሉ
በስሟ ቀን ግፊያ
“አለች አሉ አህያ”
ብለው ሲደልሏት
ሲያነሱ ሲጥሏት በተራ በተራ
በኑረት ግፍተራ፣ ለተረት ሲሾሟት
ለሽሙጥ ሲድሯት…
 
በክፋት ታጭቀው በምሬት ሲያጉላሉ
ኖረው ኖረው መጡ
ስጋዋን ሊቆርጡ፣
ጌታዋን ሊረግጡ።
* * *
አህያማ ሞልቷል “አልጋ ሲሉት አመድ”
አቀማመጥ ጠፍቶት፣ ሰርክ የሚወላገድ፤
 
ወግ ደርሶት ገራፊ ወፌ ወፌ ላላ
ከፈሱ ተጣልቶ ሰው ገድሎ ሚበላ
ከባዶ አፍ ነጥቆ ቀፈቱን ሚሞላ፤
 
“ሰው መሳይ በሸንጎ”
በየወንበሩ ላይ፣ በየቢሮው ባልጎ
“በወል ስም” ተጠሪ፣ ኗሪ ተሸሽጎ።
 
/ዮሐንስ ሞላ/
 
donkey_export_ethiopia
Fortune: Ethiopia is to export donkey’s meat, following the start of operations at a slaughterhouse in Bishoftu (Debrezeit) town, 48Km east of Addis Abeba.

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s