ሲለፋ የኖረው በሸክም በዱላ
የአህዮቹ ገላ
ቀረበ ተልኮ፣ በጀማው ሊበላ
ታጨ ለስል ቢላ።
* * *
ተርፏቸው ሳይሰጧት
“ማር አይጥማት” ሲሉ
በስሟ ቀን ግፊያ
“አለች አሉ አህያ”
ብለው ሲደልሏት
ሲያነሱ ሲጥሏት በተራ በተራ
በኑረት ግፍተራ፣ ለተረት ሲሾሟት
ለሽሙጥ ሲድሯት…
በክፋት ታጭቀው በምሬት ሲያጉላሉ
ኖረው ኖረው መጡ
ስጋዋን ሊቆርጡ፣
ጌታዋን ሊረግጡ።
* * *
አህያማ ሞልቷል “አልጋ ሲሉት አመድ”
አቀማመጥ ጠፍቶት፣ ሰርክ የሚወላገድ፤
ወግ ደርሶት ገራፊ ወፌ ወፌ ላላ
ከፈሱ ተጣልቶ ሰው ገድሎ ሚበላ
ከባዶ አፍ ነጥቆ ቀፈቱን ሚሞላ፤
“ሰው መሳይ በሸንጎ”
በየወንበሩ ላይ፣ በየቢሮው ባልጎ
“በወል ስም” ተጠሪ፣ ኗሪ ተሸሽጎ።
/ዮሐንስ ሞላ/

Fortune: Ethiopia is to export donkey’s meat, following the start of operations at a slaughterhouse in Bishoftu (Debrezeit) town, 48Km east of Addis Abeba.