ፈተናዎች…

የዛሬ 8 ዓመት ገደማ፥ በወርሀ ሰኔ፣ “ገሳ ልልበስ፣ መሬት ልረስ” በማይባልበት የሀዋሳ ከተማ፣ ከሞኝ አበስብስ ዝናብ ጋር ተሯሩጬ፥ አልፎ አልፎ፣ ከመደበኛ የቢሮ ሰዓት በኋላ፣ ከጥቂት ወዳጆች ጋር ተሰብስበን የበጎ ፈቃድ ሥራ የምናግዝበት፥ በቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሥር በተቋቋመ የምግባረ ሠናይ ኮሚቴ ቢሮ ውስጥ ገባሁ።
 
በወጨፎ የቆሸሸ ሱሪዬን ማራገፍ፣ በዝናብ የራሰ ፀጉሬን መጠራረግ እንደጀመርኩ አንዲት ህጻን እያለቀሰች ገባች። ሹራቡ የተተለተለ ዩኒፎርም ለብሳለች። በዝናብ የረጠቡ ደብተሮች በቀኝ እጇ ከደረቷ ጋር አጣብቃ ይዛ፣ ከእንባዋ ጋር ተቀላቅሎ ሊወርድ የሚለውን ንፍጧን ሳብ እያደረገች ታለቅሳለች። ከተማው ውስጥ ካሉ ቤቶች የነጻ ትምህርት ፈቃድ አግኝተን፣ ቁርስ (አምባሻ በሻይ) እዚያው ግቢ ውስጥ ተመግበው፣ ለምሳ ሽሮ ተቋጥሮላቸው ትምህርት ቤት እንዲሄዱ ከምናግዛቸው 45 የተማሪዎች መሀል አንዷ ነበረች።
 
[…ተማሪዎቹ ጎዳና ላይ ያለፈ ያገደመውን ለምነው (ሲችሉም አምታተው) የሚኖሩ ወላጅ አልባዎች፣ ወይም ከወላጆቻቸው ጋር ተጋግዘው በልመና የሚተዳደሩ ናቸው። በወቅቱ የኮሚቴው አቅም ቁርስና ምሳ ማብላት ብቻ ስለነበር፥ ከትምህርት ቤት ሲመለሱ አማራጭ በማጣት ወደልመናው ያቀናሉ። ከዚህም ባሻገር፥ ወላጆቻቸው ት/ቤት ሲሄዱባቸው የገቢ እጥረት ስለሚያጋጥማቸው፣ ልጆቹ ትምህርት እንዲያቋርጡ እንቅፋት ይሆኑባቸዋል።
 
የእኛ ዋና ሥራ፥ የማይጠቀሟቸውን አልባሳት እና ወርሃዊ መዋጮ የሚያደርጉ አባላትን ማስተባበር፣ ለዕለት ዕለት ምግብ ማብሰያ የሚወጣውን ወጪ መጠየቅ፣ እንደ ዩኒፎርም እና ደብተር የመሳሰሉ ዓመታዊ ቁሶችን ጊዜያቸው ሲደርስ ማሟላት፣ እና ህጻናቱ ወገንተኝነት እንዲሰማቸው፣ በትምህርትም እንዳይዘናጉ ‘አለሁ’ የማለት ያህል ነበር። ለምግብ ሥራው የተቀጠረ ሰራተኛ ነበር። ከበጎ አድራጊ በተገኘ የቆርቆሮ እና የሰራተኛ ክፍያ ድጋፍም ኩሽና እና ለመመገቢያ መጠለያ እንዲሆን እንደነገሩ ተመቷል። ሥራው መንፈስን ቢያጽናናም፣ በውስጡ መፈጠርን የሚያስመኙ ብዙ ፈተናዎች ነበሩት…]
 
በትምህርቷም ምስጉን ሆና፥ ለሽልማት የወላጆች ቀን ጥሪ ሁላ መጥቶልን ያውቃል።
 
“ምን ሆነሽ ነው?” አልኳት፥ ‘ይህኔ አንዱ ጥጋበኛ ሰካራም መቷት ይሆናል’ ብዬ ግምቴን አስቀድሜ።
 
የሹራቧን እጅጌ ሰብስባ በመዳፏ ይዛ፣ በአይበሉባዋ ዐይኗን እየጠረገች “ደብተሬን ዝናብ አጠበው” ብላኝ እሪታዋን እንዳዲስ አቀለጠችው።
 
“አይዞሽ በቃ፣ ሌላ ደብተር እሰጥሽና ትገለብጪያለሽ” አልኳት።
 
“ፈተና ደርሷል። ገልብጬ አልደርስም።” ብላ እዬዬዋን ቀጠለች። ምን ይደረጋል?
 
በሌላ ጊዜ እንዲሁ አንድ ልጅ እያለቀሰ መጣ። እናት የሞተችበት ያህል ነው የሚያለቅሰው። “ምን ሆነህ ነው?” ሲባል፥
 
“አባቴ ዩኒፎርሜን ሸጦ ጠጅ ጠጣበት” አለን።
 
እንዲህ ያሉ ብዙ ዓይነት ፈተናዎች ነበሩ።
 
ዩኒፎርሙን ደብቃ፥ “ጠፋብኝ ብለህ ተቀበል” ብላ የላከችም እናት ገጥማን ታውቃለች። ተስፋ ማየታቸው ሲታይ ግን ለራስም ትልቅ ተስፋ ይሰጥ ነበር።
 
18601528_1723104617701544_1109331304_nይሄ ትዝ ያለኝ፥ ሰሞኑን በVOA Amharic በኩል ከወደ ሀረርጌ የሰማነውን የመምህር ተስፋ አለባቸውን 40 ልጆችን ከጎዳና አንስቶ፣ ከሆቴል በተራረፈ ምግብ ወደ ትምህርት ቤት የመላኩ ቢያስደንቀኝ ነው። ልጆቹ የተረጂነት ስሜት እንዲያድርባቸው የማይፈልገው ተስፋ፥ የጠየቀው ነገር፣ ለልጆቹ ቋሚ ገቢ ማግኛ እንዲሆን የእንጀራ መጋገሪያ ምጣዶች እና የልብስ ማጠቢያ ማሽኖች እንዲገዙለት ነው። ከ4 ቀናት በፊትም፥ ከሌሎች ወዳጆች ጋር ሆነን የጠየቀውን ገንዘብ እና ተጨማሪ የ6 ወር ወጪ ይሆናል ያልነውን ለማሰባሰብ የgofundme ገጽ (https://www.gofundme.com/40-dreams-40-hopes-one-donation) ተከፍቶ ይህ ጽሁፍ እስከተለጠፈበት ጊዜ ድረስ፣ በ65 ሰዎች መዋጮ $3,590 ማግኘት ተችሏል። (ሊንኩን ተከትለው ሙሉ ታሪኩን ያንብቡ።)
 
ዕቅዱን ለማሳካት የቀረው እንዲሟላ፣ የምትችሉ ከ$5 ጀምሮ በማዋጣት ልጆቹን “አይዟችሁ፣ በርቱ” እንበላቸው። ያልቻላችሁ፣ በማትችሉበት ሁኔታ ያላችሁ ደግሞ፥ መልእክቱን SHARE ብታደርጉት፣ ሌላ አቅምና ሁኔታ የሚፈቅድለት ሰው አይቶት እንዲያግዝ ምክንያት ትሆኑታላችሁና፥ አደራ!

Adey/አደይ

The fusion of Paul Simon’s ‘Under African Sky’ with ትግርኛ (Tigirigna) beat, in a lyrical theme of recounting mothers in mother land (Ethiopia) and the other way round, is priceless. I am listening it on repeat. Plus, as tomorrow is #mothersday, herewith, I would like to invite you join in my cd-concert 🙂
 
Our mothers are kingdoms of our joys, queens of our lives, and crowns of our lifetime triumphs. As Marcus Garvey express mothers on his poem ‘The Black Women’ (he either, recounting them with in mother continent (Africa), they are our “black queen of beauty; goddess of Africa, nature’s purest emblem”. It is long rooted that we relate our mothers with our mother land.
 
So, when we say ‘happy mother’s day’, we also mean ‘happy mother land’ that we all deserve to see a place where people of the world can live happy, as everything has been safe in our mothers’ embrace. We all should defend humanity! We all should say ‘NO’ to inhumanity!
10311933_565603356894035_3772060369240297996_n
“ከአፍሪካ ሰማይ ስር
እናቴ ስትወልጅኝ ገና
ዓይንሽን ሳይ
በማይለካ ፍቅር ወደሽኝ
ራስሽን ሰጠሽኝ፣ ጡትሽን
 
በችግር ተነክረሽ
በድህነት ጸሐይ ጠቁረሽ
አሳደግሽኝ
ሰው አደረግሽኝ
 
እናቴ እናቴ
እናቴ… እልሻለሁ
የፍቅር አገር፣ ቤቴ፤”
 
Happy Mother’s Day to all mothers! Happy Sunday!
 
#Ethiopia #mamaEthiopia #mamaAfrica #mamaWorld #TeddyAfro #PaulSimone #MarcusGarvey #TheBlackWoman #UnderAfricanSky
 

My mom!

17990683_1291770914277272_1972899829748209674_nShe has given me
everything she has,
and everything she hasn’t;
everything she never thought
that she would look for:
as her eternal need is
sandwiched between my nerves. 

I’m everything to her,
she buys everything in me,
and she has a faith in me
and all the hope with in me.

If not my being
is there, in anything,
it all means nothing
for her, as I am big,
bigger than the world
and than anything it could offer.
But, I am everything,
even when there is nothing. 

It is my usual perplexity that
her eyes give me wings
that I couldn’t touch;
but I see, whenever I see her,
my soul overwhelmingly swing. 

She has been the light
whenever I get in a dark
that I survived the hardness
of the darkness;
and a life saver shade,
when the sun is over my heart. 

I always have been defiant.
But, growing up,
even after prepubescence
I wouldn’t do, what she’d decry
or she wouldn’t like to be done,
and would make her heart cry;
[something, if done
that she would die to undone.]

Her soul has been
a red line that I won’t cross,
if not discussed and settled,
or unless I feel that it is good:
that I grew up caring for her instinct,
meaning ‘ታዝንብኛለች‘. 

She believes in, I didn’t,
that I am the world.
While I am not even close
to be a piece of land
that she deserves to see. 

If I smile, she would smile
if I frown, she still would smile
and try to infect me.
If she cries, the sky would,
or the sheet hold, on the bed
but I never saw. 

/Yohanes Molla/ 

Long live my mom ❤ Happy mother’s day to all mothers!

 

 

ጠዪ በከፋ ቁጥር…

581855_10151320355817546_1236470796_nምንድን ነው እሱ ስራ ፈትቶ ‘ጠላሁት’ ስላሉት ሰው መመላለስ? ከሀይማኖት እና ከአማኞች ጀርባ ላይ ወርዶ አረፍተ ነገር መስራት የማይችሉ ኢአማንያንን መምሰል? “ቴዲ ይሄን መዝፈን ነበረበት። ለኧከሌ ውዳሴ መዝፈን ነበረበት። ኧከሌን ባያወድሰው። ይሄን መዝፈን አልነበረበትም።” ብሎ እኝኝ ማለትና ገና ቴፑ ሳይከፈት ምላስና ጆሮ አሹሎ ለማብጠልጠል መደራጀት? ‘የጠላሁትን ጥላ፣ የወደድኩትን ውደድ’ ብሎ ነገር ነውር አይሆንም? ‘እከክህን ትተህ የእኔን እከክልኝ’ ማለት አያስገምትም?
 
ማን ቃላት ቆጥሮ፣ ታሪክ ሰድሮ በአደራ አስረክቦታል? ማን ዜማ ሰፍሮ ሰጥቶታል? የት ከሰጠነው የሀሳብ ውሃ ልክ ነው ፈቀቅ አድርጎ መሰረት የጣለው? የትኛው የማዕዘን ድንጋይ ተናጋብን? በራሱ ፈቃድ፣ በራሱ ድምጽ፣ በራሱ ጊዜ፣ በራሱ ስም፣ በራሱ ገንዘብ ያሳተመው ሆኖ ሳለ፥ “ልጋታችሁ” ያለ ሳይኖር፣ ለምንድን ነው ለኪነ ጥበብ ወይም ለራሳቸው ጆሮ ተቆርቋሪ በመሆን ሳይሆን፣ በመንገብገብ ስሜት ውስጥ ሆነው ጥላቻን የሚያቁላሉ እና ክፋት የሚፈተፍቱ ሰዎች ከመካከላችን ሊፈጠሩ የቻሉት?
 
“ከዚህ በላይ ማድረግ ይችል ነበር። እንዲህ ቢሆን፣ እንዲያ ቢሆን… እዚህ ጋር ልክ አይደለም፣ በተሳሳተ መልኩ ነው የተገለጸው።” እያሉ በቀናውና ሰሪውንም፣ የሰሚንም ጆሮ በሚያንጽ መንገድ አስተያየት መስጠት፥ ሰሪውን ያሳድጋል፣ ለአድማጮችም የተሻሉና ዘመን ተሻጋሪ ሥራዎች እንዲሰሩ ያበረታልና መልካም ነው። በተለይ ከባለሞያ ሰዎች ይህንን እንጠብቃለን። (የጭፍን አድናቂ ስድብ ዶፍ ከባድ ቢሆንም በትንሽ ትንሹ መጋፈጥ ቢቻል እመኛለሁ። ባለፈው Abraham T. Woldemichael ቪኦኤ ላይ የሰጠውን አስተያየት ተከትሎ ዘለፋና ሙገሳ ያዘነበው ሰው አብዛኛው ቃለ ምልልሱን ያልሰማ እንደነበረ ስታቲስቲክሱን አይተናል።) ገንቢ የትችት ባህል ቢዳብርልን፣ ለሰራውም ሰው እውቅና መስጠት፣ ለሚመጣውም ትምህርት ይሆናል።
 
በሌላ ጎኑ፥ ከእነሱ የተለየ አስተያየት የሚሰጥን ሰው በስድብ እና በዛቻ የሚሞልጩ ሰዎችንም አወግዛለሁ። የምንወደውን ሰው በስድብ ካልሆነ ማስከበር የማንችል የሚመስለን ለምንድን ነው? ነፍሱስ ሰላም አታጣም? ማንስ ሰው ቢሆን፥ በርሱ የመጣ ሰዎች ሲሰደቡ እና፣ “አንተን ላወድስህ ኧከሌን ሰደብኩልህ” ተብሎ ይሸማቀቃል እንጂ ይደሰታል? ለምን የምናደንቀውን ሰው ለማሸማቀቅ እንደክማለን? ምን ይጎልብናል ሰው ያመነበትን ነገር እና የመሰለውን አስተያየት ቢጽፍ/ቢናገር? ደግሞ ምን አንገበገበን፥ የወደድነው ሰው ከዚህ በላይ የላቀ አቅም ላይ ቢደርስ?
 
ይህ በእንዲህ እንዳለ፥ ለሁሉም ነገር ጊዜና ሁኔታ አለው። እሱን መጠበቅ ተሰሚነትን ከፍ ያደርጋል። ሲቻልና ሰሪው ፈቅዶ ሲያሳትፍ፥ ቀደም ብሎ አስተያየት መስጠት ነው። ካልሆነ ደግሞ ለቀጣይ ሥራ መማሪያ እንዲሆን ከስሜት ውዥንብር አርፎ መሬት እስኪያዝ ድረስ መጠበቅ ነው። ሙሽራን የሰርጓ ቀን አዳራሽ ውስጥ ሆና “ቬሎሽ ተንዘላዘለ፣ ሜካፕሽ በዛ” ብትባል ፎቶዋ እንዲበላሽ ከመጣር ያለፈ ሆኖ የሚፈይድ ነገር አለ?
 
በቃ የተመቻቹን መርጣችሁ ስሙ። ካልሆነም ላሽ በሉ። “አድናቂ ነን” ያላችሁም፥ ውዳሴ በመጻፍ ፋንታ፣ ሌላን ሰው በመስደብ የምትወዱትን ሰው ክብር ለማስጠበቅ አትሞክሩ። ትገመታላችሁ። ሁሉንም ሰው ካለምንም ተቆርቋሪ ስራው ያወጣዋል። ማንም ማንንም አያቆምም፣ አያራምድምም! ማንም በሰው ማጥላላት እንቅስቃሴውን አላቆመም። ማንም በወዳጆቹ ተሳዳቢነት ጸንቶ አልበረታም።
 
ጠዪ በከፋ ቁጥር ፍቅር በአምባው ላይ ይገናል! ልክ እንደዚሁ፥ ፍቅር አጨማልቆ እና ጨፋፍኖ፣ ልዩ የሆኑትን ማሳደብ ሲጀምር ተደናቂው ሰው ላይ ጭምር ጥላ ያጠላል። በፍቅር አምባገነንነት ውስጥ ግዞት ያለን ሰው ከስሜቱ እኩል እልህ ይዘውረዋል። ጥላቻም እንዲሁ ነው።
 
ስለዚህ እንተሳሰብ ጓዶች! ተቃቅረን ከምንኖር የተወሰኑ እርምጃዎችን ተቀራርበን የጋራ የሀሳብ ነጻነት ቤታችንን እንገንባ። ቢያንስ ፌስቡክ ያለውን ዘርፈ ብዙ ተጽህኖ እያየን ነውና፥ ፌስቡክ ላይ እንበርታ። ልክ እንደበፊቱ እንማማርበት።
 
ኢትዮጵያ ውስጥ ተቀብሮ ባለው እና ተከብሮ በዋለው ዓለማቀፍ የፕሬስ ነጻነት ቀን፥ ይህንን ስናገር ደስታ ይሰማኛል! 😉
 

Aging…

A_Woman_Looking_In_the_Mirror_At_Her_Wrinkled_Face_Royalty_Free_Clipart_Picture_100224-119323-928053Growing older has never been an easy phenomenon though it has been long and ardently awaited, much bragged about, and celebrated. Hadn’t it been corrupted, it should get due attention as teenage does.
Karma becomes more complicated with aging than it was ever. The World and it’s treasures – that were handful of our desires and joys in childhood, our ambitions to discover in prepubescence, and rebellion character in adolescent – gets to be infinite; and we want it all in vain that we stretch our hands to every direction, but we catch almost nothing. Our guts as a young to catch the fire gets down to inability to catch even the wind.
We know many people and many topics roughly, we socialize with many souls, but we feel that we have lost the grace; and yet, deep down, we want to selectively filter our circles… and we even are not close to what we want to know, and the kind of life we want to have. In fact, we know so much, but we ruin it all seeing what is not there. It is a different kind of complex and/or curse that we get pissed of against any kind of thing that reminds the fact that we are aging.
We try, we count our failures. We get prepared too much, we see our sweats. We want to laugh, we see the moments that we’ve wept. We want to shine, we stare at our wrinkles. We wish to keep our hair in style, but we see it balder and grayer. At times, we even laugh looking into the cosmetics we have bought. But when it comes to publicity, we change it all upside down and want to magnify the goods in us – that hasn’t been covered in the first place – at the cost of silencing youth. There will come fight within ourselves, and between emerging souls.
We, optionlessly and as a good virtue, become very specific to our activities, interests, and involvements, while we know many in general. And yet, at the eve of our adulthood and while on it, we find it hard to goodbye our youthhood. We rather live swinging between nostalgia and proving right that we are fine with the status quo.
We used to enjoy the moments… but as getting older, we preach much than we live; we speak more than we do; we talk more than we listen; we recall way less memories than we lived. We want to bury the young souls in the skin of our memories. We want to sing and let others about what was, than urging to fight for what is.
Regret couldn’t leave us alone; nor does ego. Time flies like were never before. Life becomes in a fashion of coffee and bear, and with bittersweet memories. Whatsoever, we die while explaining and proving ourselves right.
We can’t help it, with aging, life changes so fast, and memories fade away one by one. More powerful and wonderful minds are taking over our places. Time slip away things that we valued most, and our strength.
People become scared of being attacked personally; thus, they think they can skip from it by doing it on others. People start hating being judged, but they can’t stop hiding them selves in judgementalness. Fraternity and racism are most talked about topics, but few happen to be racist.
Good Lord!