ጋሽ ስብሀትን አንድ ጋዜጠኛ
“ከቅርብ ጊዜ ዘፋኞች የምትወደው” ሲለው
“ይኼ ነይልኝ…የሚለው ልጅ ይመቸኛል“
ጋዜጠኛው ቀጠል አድርጎ
“የማይመችህስ ዘፋኝ?” ሲለው
“ከእሱ እየተቀበለ “ነይለት” የሚለው አቃጣሪ” አለው አሉ።
ይኼን ያስታወስኩት ዮሴፍ ገብሬ (ጆሲ) እና ያ ቀልማዳ ልደቱ አያሌው ያወሩትን ዞር ዞር ብዬ ተመልክቼው፥ አንዴ ጆሲን፣ አንዴ ልደቱን እያልኩ መመዘኑ ሰለቸኝና ነው።
ቃለ መጠይቁ ሲጀምር እና “የፍቅር እስከ መቃብር ደራሲ ማነው?” በሚል ጥያቄ ነው። ተመልካቾች በ2 ብር (?) የጽሁፍ መልእክት ሰዎች ምላሽ እንዲሰጡና፣ ከመካከላቸው አንዱ ስጦታ እንደሚበረከትለት ይገልጻል። ማስታወቂያው በየመሀሉም ለብዙ ጊዜ ይደጋገማል። የመጀመሪያው መላሽ ለሚሸለም ያን ያህል መደጋገሙስ ለምን አስፈለገ? ማለቴ አልቀረም። በሁለተኛው ክፍል ደግሞ ጥያቄው “ይኽች አርቲስት ማን ትባላለች” ብሎ የእንግዳዘርን ምስል ነው የሚያሳየው።
ብቻ ሕዝቤ በነፍስ ወከፍ ሁለት ሁለት ብሯን አዋጥታ ታበረክታለች። ይመቻቸው!
የመጽሐፍ ነገር ሲነሳ፥ የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ሳለው መምህሬ የነበረና፣ አሁን የቅርብ ወዳጄና አማካሪዬ ጋር ከሳምንታት በፊት ስናወራ በጨዋታ መሀል ያነሳብኝ ነገር ትዝ አለኝ።
ከወዳጄ ጋር የነበረን ጨዋታ፥ እንደአገር ስላለመታደላችን፣ ይኽ ነገር የሚቆምበት ጊዜ እንደሚናፍቀን፣ እንዲሁም ድርሻችንን ለመወጣት በየዙሪያችን ራስን ከመለወጥ አንስቶ መሞከር እንጂ፥ የሚታይ የሚሰማው ነገር ሁሉ ተስፋ አስቆራጭ ስለመሆኑ ነበር። ነገርን ነገር አንስቶት ወዳጄ ጆሲን አስታወሰው።
“በጣም ነው የሚያሳዝነው። የሚዲያ ባለቤት እንኳን ለእፍረት ብሎ ስለንባብ የሚገነባ ነገር አያወራም።
አሁን ባለፈው ጆሲ የሚሉት ልጅ ከአንድ ሌላ ጋዜጠኛ ጋር ያወራል። ጋዜጠኛው “መጽሐፍ ታነባለህ ወይ?” ብሎ ይጠይቀዋል።
“አሁን አላነብም። ድሮ ግን አነብ ነበር።” አለው ኮራ ብሎ።
“እስኪ ድሮ ካነበብካቸው መጽሐፍት ያንዱን ርዕስ ንገረን” ሲለው፥
“አሁን ትዝ አይለኝም።” አለው።
ምናለ የአንዱን መጽሐፍ ርዕስ እንኳን ቢጠራ? ቢቀር ፍቅር እስከ መቃብር አይልም ሰው? እንግዲህ ይኽ የሚዲያ ባለቤት፣ ጋዜጠኛ እና ዘፋኝ ነኝ የሚል ሰው ነው። ሌላውን ደግሞ አስበው።” ተባባለን፣ መዓዛ ብሩን አወድሰን አለፍን። (ባይጠቅመኝም ሌላ ቃለ መጠይቁን የሰማ፥ ወይ ከማን ጋ እንደሆነ የሚያስታውስ ካለ ቢነግረኝ እና ብሰማው ደስ ይለኛል።)
መዓዛ ብሩን ስናወሳ ስለእንግዶቿ ያላትን ጥልቅ እውቀት እና፣ ስለሰሩት ነገር ለማወቅ ጥናት/ምርምር ስለማድረጓም ጭምር ነው።
ይኽን ማንሳቴ ደግሞ ጆሲ ስለእንግዳው እንዴት ጥናት አያደርግም? ቢያንስ ከጻፋቸው መጽሐፍት አንዱን በወፍ በረር ቃኝቶ ማውራት ቢቀር፥ እንዴት ስለመጽሐፎቹ እሱ እንዲናገር እንኳን የመጽሐፉን ወሬ አያነሳበትም?
ጭራሽ ስለመጽሐፍና ንባብ፣ ስለጻፈው ልብወለድ ሲያነሳበት ሁሉ፥ የጆሲ ልብ ፔጆዋ ላይ ነው ጆፌ ብላ የቀረችው።
ብቻ ያው ነው።
ጆሲ “ሰማሁ… አሉ…”
ልደቱ “አልኩ… አደረግኩ… እኔ መሲሁ ነኝ። ልወደድ አልልም። ሕዝቡ ይወደዋል አይወደውም አልልም። እኔ ካመንኩበት እናገረዋለሁ።”
ያው መበጣረቅ ነው!
ሕዝብ ካልወደደው ለአገር ምኑን ጠቀመ? “አገር ማለት ሰው ነው” እንደሚባል አያውቅም ማለት ነው? ለነገሩ፥ ቤቴ ውስጥ ይሉኝታ ያጠቃኛል። በፖለቲካ ግን ይሉኝታ አላውቅም ብሎ ነገሩን ሲጀምር ነበር ማቆም የነበረብኝ።
የተቸገርነው እኮ አገሪቱን እንደቤታቸው አላከብር እያሉን ነው። ሕዝቡን እንደወገናቸው አልቆጥር እያሉን ነው።
ይኽን ስጽፍ ፌስቡክ “የዛሬ ዓመት ምን ብለህ ነበር” ቢለኝ ጥሩ ነው?
እንደው… የሞት የሽረት “ግድ መምረጥ አለብህ” ብባል፥ አይደለም ከሌላ ሌላው…
“መለስ ዜናዊ ከልደቱ አያሌው ብዙ ጊዜ ይሻለኛል!” እላለሁ! Period! ብለህ ነበር ይለኛል።
ምድረ አተቲያም፥ “የአረም እርሻ” ገበሬ! ጆሲን ግን ጥሩ ለጎም ለጎም፣ ጎተት ጎተት አድርጓታል። ሃሃሃ…
እኔማ ከ1992 ዓ/ም (ለመጀመሪያ ጊዜ ቲቪ ላይ ካየሁት ጊዜ) “ሆኜ፣ ተደርጌ” ሲል ሰምቼው እንደቀፈፈኝና ቀልማዳነቱ ብቻ እንደሚታየኝ አለ። He is one of the persons/things that time and time prove my instinct right.
ሃሌሉያ!