ስለ24 ዓመቷ ሌንሴ ኔሜ ሹመት

 

43371204_2460431533973313_7357390166161358848_n

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስኪያጅ (CEO) ተደርጋ የተሾመችውን፣ የ24 ዓመቷን ሌሊሴ ኔሜ በተመለከተ መረጃውን ማጋራታችንን እና ነገሩን ማውገዛችንን ተከትሎ፣ በግራም በቀኝ ወዳጆች አስተያየት ሰጥተዋል።

 
ነገሩ ያስቆጣቸው በርካቶች የመኖራቸውን ያህል፣ በገራገርነት ተመልክተው “ከቻለች ምን ችግር አለው? ወጣት ወደ ሀላፊነት ሲመጣ ማበረታት ነው ያለብን” ዓይነት ሀሳብ የሰጡም አሉ።
 
ከዚያም አልፈው፣ ጽሁፉ ኦሮሞ ስለመሆኗ በማይገልጽበት ሁኔታ፥ “ገና ለገና ኦሮሞ ስለሆነች፤ የኦሮሞ ስም ስላላት” ብለው በልባቸው የሚያስቡትን (ምናልባትም እየሆነ ያለውን ስለሚታዘቡ) የተናገሩም አሉ።
 
ባረጀ ባፈጀ ማሸማቀቂያ “ኦሮሞፎቢያ” ያሉም አሉ። እንደዚህ እያልን እውነትን የምናፍንበት እና የምናሳቅቅበት ጊዜ ሳያልፍ አልቀረም። ስለኦሮሞነቷ ነው ብሎ ከማሰብ ይልቅ፣ “ከእሷ የተሻለ ለቦታው የሚበቃ ኦሮሞ ስለሌለ ነው ወይ?” ብሎ መጠየቅስ አይቀልም ነበረ? 
 
አሁን ማንሳት የፈለግኩት ግን ነገሩን በበጎ ተመልክተው “ምን ችግር አለው? ዋናው ብቃት ነው እንጂ ዕድሜ አይደለም። እስከቻለች ድረስ ትሁና።” ያሉትን ነው።
 
በመጀመሪያ እንደዚህ ያለ አገር አቀፍ ዋና ፕሮጀክት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሀላፊ (CEO)
መሆን ከልምድም ከእውቀትም አንጻር የሚጠይቀው ብዙ ነገር አለ። የነገሩን ትርጓሜ፣ የሚሰጠውን ሀላፊነት እና ዓለም ላይ እንዴት ነው የሚስራበት የሚለውን መፈተሽ ተገቢ ነው።
 
ብስለት እና አመራር ጋር ሲመጣ፣ ዕድሜ ቁጥር ብቻ አይደለም። የሚያሸክመው ልምድ፣ እውቀትና ብስለትም አለው። 24 ዓመት ተለዋዋጭ ፍላጎት እንኳን ጠርቶ ቦታ ይዣለሁ የማይልበት፣ ከራስ ጋር ተስማምተው የማይጨርሱበት ዕድሜ ነው።
 
እንደዚያ ባይሆን እንኳን፣ ከተመረቀች 2 ዓመት የሆናትን ወጣት ለዚህ ቦታ ለመሾም፣ መስፈርቱ እሷ የምታሟላውን ያህል ብቻ ሲሆን ነው። ካልሆነ ግን ቢያንስ ያስተማሯትም አሉና፣ የት ባሳየችው የአመራር ብቃት ነው ተመራጭ ሆና ለሹመት የምትበቃው?
 
(በርግጥ የሌንሴ የሹመት ሙስና እና ፖለቲካዊ አድልዎ የጀመረው ከዩኒቨርስቲ ከመመረቋ በተሰጣት ሹመት ነው። እንደዚያም ሆኖ እንኳን፣ ዩኒቨርስቲ ውስጥ የማስተማር ስራዋን ሳትተው፣ ዋና ስራ አስኪያጅነቱን ደርባ መስራት መቻሏም ሌላ አነጋጋሪ ጉዳይ ነው። ካልተሳሳትኩ፣ የስራ አጡ ቁጥር ባሻቀበበት አገራችን ላይ፣ ሁለት የመንግስት መስሪያ ቤት ተቀጥሮ መስራት በህግ የተከለከለ ነው። በዚያም ላይ በእንደዚህ ያለ ከፈተኛ የአመራር ስራ ላይ ያለ ሰው፣ መኪና የመንዳትን ስራ እንኳን ደርቦ እንዳይሰራ ጥንቃቄ ይደረግለታል።)
 
ቦታው የተሰጣት በሹመት ነው እንጂ፣ ማስታወቂያ ወጥቶ ሰዎች አመልክተው፣ በነጻ ተወዳድረው እና በገለልተኝነት ተመዝነው አለመሆኑ ነገሩን ከብቃት እና ከእውቀት ጋር እንዳናያይዘው ያደርገናል። ምናልባት እርሷ የትምህርት ቤት ጓደኞች መካከል (የዛሬ 2 ዓመት የተመረቁ) የመጀመሪያ ስራ እንኳን ይዘው የማያውቁ ይኖሩ ይሆናል። በጣም ችሎታ እያላቸው፣ በፓርቲ ተሳትፎ እና ትውውቅ የተነሳ ስራ አጥተው ባክነው የቀሩ ብዙ ሰዎች እንዳሉም ይታወቃል።
 
ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ “ከቻለችው ምን ችግር አለው? ዋናው መስራቷ ነው” የሚሉት አስተያየቶች ናቸው፣ ሌላ ትኩረቴን የሳቡት።
 
ታዲያ ትናንትና “የትግራይ የበላይነት ነገሰ” ያልነው ለምን ነበር?
 
አንድ መስሪያ ቤት ውስጥ ከጥበቃ እስከ ሀላፊ ድረስ ትግሬዎች ናቸው የሚቀጠሩት እና ቦታ ቦታ የያዙት የተባለው ለምንድን ነው?
 
ኮንዶሚነም ቤት እስከከፈሉ ድረስ ቢሰጣቸው ምን ችግር ነበረው?
 
የጥበቃ ሰራተኛው እስከጠበቀ ድረስ ትግሬ ሆነ ምን ሆነ ለምን ደነቀን?
 
የመከላከያ ሰራዊቱ ብሔር ስብጥር ለምን አሳሰበን?
 
የአውሮፕላን አስተናጋጇ እስካስተናገደች እና አውሮፕላኑ ስራ እስካላቆመ ድረስ፣ ትግሬ ሆነች ምን ሆነች ምን አገባን?
 
መርካቶ ንግዱ እስካልታጎለ ድረስ፣ ጉራጌዎችን አፈናቅለው በግብር እና በኮንትሮባንድ ደግፈው ትግሬዎችን ቢያስፋፉ ምን አስጨነቀን?
 
የተለያዩ ሀላፊነት ቦታዎች ላይ የተሾሙትስ አለመቻላቸው በምን ታወቀና ነው ትግሬ መሆናቸው ያስከፋን?
 
ታዲያ ድካማችን ሁሉ ለምን ነበር?
 
አገሪቱ ላይ ሁሉም ዜጋ እኩል ተጠቃሚ ይሁን ከሚል ቅንነት አይደለምን? ፍትህ እና ተጠያቂነት እንዲነግሱ፣ የዘመድ እና የካድሬ አሰራር እንዲወገድ አይደለምን?
 
“አዲስ ንጉስ እንጂ ለውጥ መቼ መጣ” የሚለው ሙዚቃ ትዝታ ይሁንልን! የትናንቱን የጠላነውን፣ በአዲስ ዛሬ ለመተካት አይደለም ተስፋ እና ጉጉቱ!
 
ኢፍትሀዊ አሰራር ይውደም!

ቤቲ እና ደሳለኝ፡ እንደወረደ! :)

የቤቲን እና የዶ/ር ደሳለኝን ቃለ መጠይቁን አየሁት። የተባለውን ያህል የተጋነነ ሆኖ ግን አላገኘሁትም። ደሳለኝ አለመዘጋጀቱ ያስታውቃል። መዘጋጀት ሲባል፣ ለቃለ መጠይቅ ሳይሆን፣ በአጠቃላይ እንደ ፓርቲ አመራር ራሱን በብዙ ነገሮች ውስጥ ማለማመድ እና ነጥሮ የወጣ ሀሳብ/መልስ የሚሆን ነገር ማዘጋጀት ነበረበት። አባላቱም እንዲሁ ማድረግ ነበረባቸው። ለከእንግዲውም መዘጋጀት አለባቸው።
 
በዋናነት ደሳለኝን የማይሆን ነገር ውስጥ የከተተው ጋሻው እና ክርስቲያን የተባሉ ስራ አስፈጻሚ አባላቶቹ ያደረጉትን ያልተገባ እና ያልበሰለ ንግግር ለማስተባበል እና “ማለት የፈለጉት” እያለ፣ ያላሉትን ሊልላቸው እና ያሉትን ሊያለባብስላቸው ባደረገው ጥረት ነው።
 
ከዚህ የምንማረው/የምንረዳው፣ አባላቱ (እንዲሁም ሌሎቻችን) ከፌስቡክ ወጣ እያሉ ወደ መጽሐፍት ገጾች አየት ማድረግ እንዳለባቸው ነው። እሱም ዐይኑን ያፈጠጠ፣ ጥርሱን ያገጠጠ ነገርን በይቅርታ ማለፍ ቢችል ተወዳጅነት እንደሚጨምርለት ከዶ/ር አብይ ኢህአዴግ መማር ይቻላል።
 
አብን ገና የሶስት ወር ጨቅላ ፓርቲ እንደመሆኑ መጠን ክፍተቶች ቢታዩ ብዙም ባያስደንቅም፣ ችኩል ችኩል እያሉ የፈጠሩትን ስህተት፣ “ሌላው ሰው ካለበት የመረዳት ችግር የተነሳ ነው እንጂ እኛ ልክ ነን” ማለት ወዳጅ እና ደጋፊ ያሳጣል እንጂ ሩቅ አያስኬድም። ከአሁኑ ያልተጀመረ ይቅርታ የመጠየቅ እና ራስን የማረም ባህልም፣ ውሎ አድሮ ስለመቀጠሉ መተማመኛ አይሰጥም።
 
ነገሮች በግልጽ ለክርክር እና ቅሬታ ክፍት በሆኑበት ቦታዎች/ሁኔታዎች “ስህተት ነበር። ይቅርታ። እንዳይደገም እንመክርበታለን።” ብሎ ማለፍ እየተቻለ፣ ባስረዳው ቁጥር የማይሆን ነገር ውስጥ ራሱን ከቷል። በዚህም፥ ከ27 እስከ 48 ደቂቃ ያለው ጊዜ በከንቱ እና ራሱን በማሳጣት የባከነ ነው። ልክ እንደዒድ በዓል መልካም ምኞት መግለጫው “ሌላን ሰው ካስከፋ ይቅርታ” ብሎ በሰላም እና በክብር አልፎት፣ ሀሳቦቹን ማስረጽ እና ሀሳብ ላይ ማውራት ይችል ነበር።
 
ደሳለኝ ምናልባትም ፓርቲውን (የፓርቲውን ስም) ለማስተዋወቅ ያህል ጥሩ እድል አገኘሁ ብሎ የሄደ ዓይነት ይመስላል። እሱ ደንገጥ ሲል እሷ በስሜታዊነት እየተናጠች ኮስተር ማለት መጀመሯ ነጻ ጋዜጠኛ የማያስብላት ነው። ጭራሽ ልትቆጣው ሁሉ የሚያምራት ቦታ አለ። ደካማ ጎን ያገኘች እየመሰላት፥ የልብ ልብ እየተሰማት፣ እንደ ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ፀጋዬ ለመሆን የፈለገችባቸው ቦታዎች ብዙ ናቸው።
 
እንደ ቃለመጠይቅ አድራጊነቷ እውነቱን እና ሀሳቡን መፈልፈልና ማውጣት ላይ እንጂ፣ የእሷን ሀሳብ ወይም መከላከያ እና ቅሬታ ማከል ላይ ማተኮሯ ለመደበኛ ቃለመጠይቅ የሚያስኬድ አይመስለኝም። ያም ሆኖ ግን፣ እንደፈለገች አድርጋ መጠየቅ መብቷ ነው። ሊያሰድባት የሚያደርስ ነገር የለም።
 
የተከፋ ሰው፥ ፕሮግራሞቿን አለመስማት፣ ወይም ደግሞ እሷ ጋ ቃለ መጠይቅ አልደረግም ብሎ ሊያምጽ ይችል ይሆናል፣ እንጂ “ሊቀመንበሬን ይህን ጠየቅሽብኝ፣ አጨናነቅሽብኝ” ብሎ የተሳደበ አባል ወይም ደጋፊ፥ እድሉን ቢያገኝ ልሰር ልግረፍ ማለት አያምረውም አይባልም እና “ሳይቃጠል፣ በቅጠል!” ነው መሆን ያለበት።
 
በየመሀሉ እየገባች በተነሳው ነገር ላይ ሁሉ ከኦሮሞ ጋር ማነጻጸሯም በአስፈላጊ ቦታ የሆነ አይደለም። ራሷንም ወደ ኦሮሞ ብሔር ያዘነበለች አድርጎ ያሳያታል።
 
ነገሬ ብላ ፓርቲውን ማሳጣት ላይ ወይም ራሷን እነደሀይለኛ ማስቆጠር ላይ ማተኮሯን የሚያሳይ፣ መሀል ላይ በቃለመጠይቁ ወቅት ያለተጠቀሰ እና ካለደሳለኝ እውቅና የተሰነቀረ የልማታዊ አርሶአደሮች ምስል አለ። በመንግስት የሚደገፈው የአማራ ክልል ቴሌቪዥን (መቼቱ አልተጠቀሰም) ለፕሮፖጋንዳ ያደረገውን ቃለ መጠይቅ እንደማስረጃ መሰንቀሯ ሳያንስ፣ እሱ ተመልክቶት ምላሽ እንዳይሰጥበት ማድረጓ የሙያን ስነምግባር ያጓደለ መሰለኝ።
 
ደሳለኝም ቢሆን “ውሻ በቀደደው ጅብ ይገባል” እንዲሉ፣ እሷ በጀመረችው ማነጻጸር ገብቶ ‘ፓርቲው የተቋቋመው፣ እና የምናደርገውን ሁሉ የምናደርገው ሌሎች ስላደረጉት ነው’ ዓይነት ገደምዳሜ ላይ እንድንደርስ የገፋፋን ይመስላል።
 
የአማራ ፓርቲ ሊቀመንበርነት፣ ፓርቲው ለመደራጀት ገፊ የሆነውን ምክንያት የስሙን ያህል፣ በጥናት እና ንባብ ተደግፎ አጣፍጦ ማስረዳት ይጠበቅበታል/ት ነበር። ቢያንስ ስለፕሮግራም ሲጠየቅ መደናገጥ የሚጠበቅ እና አስፈላጊ አልነበረም። እንጂ፣ ቢያንስ አማራ ኢትዮጵያን በመገንባት ሂደት ያበረከተውን ነገር ለመጥቀስ፣ ስነጥበቡን እና ኪነ ጥበቡን መጥቀስ ብቻውን ይበቃው ነበር።
የእድገት እና የስልጣኔ ጠቋሚ የሆኑትን የወሊድ ቁጥር መቀነስ እና ተያያዥ ዴሞግራፊክ ነገሮችን፣ እንደበደል ማቅረቡም ከምሁርነቱ አይጠበቅም። ከዚያ ይልቅ በቅርቡ እንኳን በአማራ ቴሌቪዥን ላይ የቀረቡትን የእስር ቤት አያያዝ ፕሮግራሞች ጠቅሶ መናገር ይችል ነበር።
 
የአካባቢውን የማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ሁኔታ፣ በጊዜ መዳርን ጨምሮ ሌሎች ልማዳዊ ድርጊቶች ያበረከቱትን አስተዋጾ፣ ት/ት እንዳይስፋፋ እና መሰረተ ልማቶች እንዳይከናወኑ በመደረጉ የደረሱትን ጥፋቶች፣ እንዲሁም ብዙ መውለድ ለመቀንጨር የሚያድርገውን አስተዋጽኦ እና ያም የሚያመጣውን የአእምሮ ውሱንነት ማሰብና፥ ጉዳዩን በተሻለ ማስረጃ ማቅረብ ነበረበት።
 
ወይ ደግሞ እንደ ኢህአዴግ/ብአዴን፥ ፓርቲው ዋና ዒላማ ያደረገው ገበሬውን ሆኖ፣ በአሉሽ አሉሽ እንፍሽፍሽ ማለፍ ፈልገው ይሆናል።
 
በዚህ የተነሳ፣ ማህበረሰቡ ሊደነቅበት በሚገባው ነገር ክስ ማጠናከሪያ አድርጎታል። (ልክ መስታወት ሲሰበር ይቆርጣል፤ ካዩበት ያሳያል እንደማለት ያለ፥ ነገሩን ከብዙ አንግል ማየት እና ትክክለኛ መከራከሪያ ማቅረብ ይቻላል። እኔ እንኳን ከሱ የተሻለ ይህንን ጉዳይ ማስረዳት የምችል ይመስለኛል።)
 
እሷም ጉዳዩ ላይ ንባብ ጠገብ ብትሆን ኖሮ፣ እዚህ ጋር ጥሩ ውይይት ያደርጉ ነበር። ባይሆን ግን የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ሪፖርቶች ላይ የአማራው ቁጥር አንሶ እንዲዘገብ የሚደረግበትን ምክንያት ማህበረ ፖለቲካዊ አድርጎ ማቅረብ እና ነጥብ ማስያዝ ይችል ነበር።
“በአብን ስም ያልተገባ ነገር የሚያደርጉ ስላሉ፣ ግለሰቦች ስለሚጽፉት ነገር ፓርቲው ሊወቀስ አይገባውም” ዓይነት ነገር ባለበት አንደበቱ፣ ስለእነ ግንቦት 7 ሲናገር ርግጠኛ ሆኖ “ደጋፊዎቻቸው” አባባሉም ከወገንተኝነት ያልጸዳ አቋም እንዳለው ነው የሚያሳየው።
 
ደግሞ በአብን ስም ለተደረጉ ስህተቶችስ፣ ፊት ለፊት ቀርቦ የእኛን ፓርቲ አይወክልም ብሎ ወዳጅንም ማረጋጋት፣ ጠላትንም ማስደንገጥ አይቻልም ወይ? ወይስ እንደ ኦነግ ሰው ተገድሎ፣ ሰው ተባሮ “አባላቶቼ አይደሉም። በስሜ ነው ይህን የሚያደርጉት።” ለማለት ነው የሚጠበቀው?
 
ሲመስለኝ፡
 
የአብን ነገር እንደ ትኩስ ሽልጦ “ጠዋት ተመርቶ፣ ከሰዓት መርካቶ” ዓይነት ይመስላል። ምናልባትም ዋና ግብ ያደረጉት ለመጪው ምርጫ መሳተፍ ነው።
 
የምር ለአማራው የሚቆረቆሩ ከሆነ ግን ከሕዝባዊ ስብሰባዎች እና ውይይቶች እኩል፣ ውስጣዊ ውይይቶች፣ የንባብ እና የርስበርስ ስልጠና፣ የመጽሐፍ ተዋውሶ ማንበብ ዝግጅቶችን ማድረግ ይኖርባቸዋል። ያድርጉ አያድርጉ ባላውቅም ከሚናገሯቸው እና ልዩነትን ከሚይዙባቸው ነገሮች ተነስተን፣ ክፍተት እንዳለ በግልጽ መናገር ይቻላል።
ነገሩን ጠቅለል ስናደርገው፡
 
ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ አብንን ሳይወክል፥ ስለአብንም ሆነ አማራ መደራጀት ቢጠየቅ ከዚህ የተሻለ ቃለመጠይቅ ማድረግ ይችል ነበር ብዬ አስባለሁ! ይህም የሚሆነው ከእርጋታ እና ነገሩ ላይ ከመብሰል እንጂ፣ ከግል አቅም አይደለም። ዶ/ር ደሳለኝ እርጋታውን እና ቅንነቱን አሳይቷል።
አብን እንደሶስት ወር ዕድሜው በጣም ጥሩ እየሰራ ነው! እንደ አማራ ሕዝብ ግን ገና ነው! ለሰፊው እና ስልጡኑ አማራ ሕዝብ አብን ይጠበዋል።
 
ባልተያያዘ ወሬ ደግሞ፡
 
እሱ “አብን ለሕብረ ብሔራዊ ድርጅቶች ስጋት ነው” ያላትን ወስጄ፥ ሕብረ ብሔራዊው ግንቦት 7፣ ለአብን ስጋት እንዳይሆን እንደሚፈሩ፤ አባላቱም በዚህም ስጋት የተነሳ ግንቦት7ን ማጥላላት ላይ እንደተጠመዱ ብነግረው አልጠላም።
 
በቅንነት ተደራጁ! የተደራጃችሁም በቅንነት ተራመዱ! በርቱ!
ሰላም!

እንደወረደ! ;)

የቤቲን እና የዶ/ር ደሳለኝን ቃለ መጠይቁን አየሁት። የተባለውን ያህል የተጋነነ ሆኖ ግን አላገኘሁትም። ደሳለኝ አለመዘጋጀቱ ያስታውቃል። መዘጋጀት ሲባል፣ ለቃለ መጠይቅ ሳይሆን፣ በአጠቃላይ እንደ ፓርቲ አመራር ራሱን በብዙ ነገሮች ውስጥ ማለማመድ እና ነጥሮ የወጣ ሀሳብ/መልስ የሚሆን ነገር ማዘጋጀት ነበረበት። አባላቱም እንዲሁ ማድረግ ነበረባቸው። ለከእንግዲውም መዘጋጀት አለባቸው።
 
በዋናነት ደሳለኝን የማይሆን ነገር ውስጥ የከተተው ጋሻው እና ክርስቲያን የተባሉ ስራ አስፈጻሚ አባላቶቹ ያደረጉትን ያልተገባ እና ያልበሰለ ንግግር ለማስተባበል እና “ማለት የፈለጉት” እያለ፣ ያላሉትን ሊልላቸው እና ያሉትን ሊያለባብስላቸው ባደረገው ጥረት ነው።
 
ከዚህ የምንማረው/የምንረዳው፣ አባላቱ (እንዲሁም ሌሎቻችን) ከፌስቡክ ወጣ እያሉ ወደ መጽሐፍት ገጾች አየት ማድረግ እንዳለባቸው ነው። እሱም ዐይኑን ያፈጠጠ፣ ጥርሱን ያገጠጠ ነገርን በይቅርታ ማለፍ ቢችል ተወዳጅነት እንደሚጨምርለት ከዶ/ር አብይ ኢህአዴግ መማር ይቻላል።
 
አብን ገና የሶስት ወር ጨቅላ ፓርቲ እንደመሆኑ መጠን ክፍተቶች ቢታዩ ብዙም ባያስደንቅም፣ ችኩል ችኩል እያሉ የፈጠሩትን ስህተት፣ “ሌላው ሰው ካለበት የመረዳት ችግር የተነሳ ነው እንጂ እኛ ልክ ነን” ማለት ወዳጅ እና ደጋፊ ያሳጣል እንጂ ሩቅ አያስኬድም። ከአሁኑ ያልተጀመረ ይቅርታ የመጠየቅ እና ራስን የማረም ባህልም፣ ውሎ አድሮ ስለመቀጠሉ መተማመኛ አይሰጥም።
 
ነገሮች በግልጽ ለክርክር እና ቅሬታ ክፍት በሆኑበት ቦታዎች/ሁኔታዎች “ስህተት ነበር። ይቅርታ። እንዳይደገም እንመክርበታለን።” ብሎ ማለፍ እየተቻለ፣ ባስረዳው ቁጥር የማይሆን ነገር ውስጥ ራሱን ከቷል። በዚህም፥ ከ27 እስከ 48 ደቂቃ ያለው ጊዜ በከንቱ እና ራሱን በማሳጣት የባከነ ነው። ልክ እንደዒድ በዓል መልካም ምኞት መግለጫው “ሌላን ሰው ካስከፋ ይቅርታ” ብሎ በሰላም እና በክብር አልፎት፣ ሀሳቦቹን ማስረጽ እና ሀሳብ ላይ ማውራት ይችል ነበር።
 
ደሳለኝ ምናልባትም ፓርቲውን (የፓርቲውን ስም) ለማስተዋወቅ ያህል ጥሩ እድል አገኘሁ ብሎ የሄደ ዓይነት ይመስላል። እሱ ደንገጥ ሲል እሷ በስሜታዊነት እየተናጠች ኮስተር ማለት መጀመሯ ነጻ ጋዜጠኛ የማያስብላት ነው። ጭራሽ ልትቆጣው ሁሉ የሚያምራት ቦታ አለ። ደካማ ጎን ያገኘች እየመሰላት፥ የልብ ልብ እየተሰማት፣ እንደ ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ፀጋዬ ለመሆን የፈለገችባቸው ቦታዎች ብዙ ናቸው።
 
እንደ ቃለመጠይቅ አድራጊነቷ እውነቱን እና ሀሳቡን መፈልፈልና ማውጣት ላይ እንጂ፣ የእሷን ሀሳብ ወይም መከላከያ እና ቅሬታ ማከል ላይ ማተኮሯ ለመደበኛ ቃለመጠይቅ የሚያስኬድ አይመስለኝም። ያም ሆኖ ግን፣ እንደፈለገች አድርጋ መጠየቅ መብቷ ነው። ሊያሰድባት የሚያደርስ ነገር የለም።
 
የተከፋ ሰው፥ ፕሮግራሞቿን አለመስማት፣ ወይም ደግሞ እሷ ጋ ቃለ መጠይቅ አልደረግም ብሎ ሊያምጽ ይችል ይሆናል፣ እንጂ “ሊቀመንበሬን ይህን ጠየቅሽብኝ፣ አጨናነቅሽብኝ” ብሎ የተሳደበ አባል ወይም ደጋፊ፥ እድሉን ቢያገኝ ልሰር ልግረፍ ማለት አያምረውም አይባልም እና “ሳይቃጠል፣ በቅጠል!” ነው መሆን ያለበት።
 
በየመሀሉ እየገባች በተነሳው ነገር ላይ ሁሉ ከኦሮሞ ጋር ማነጻጸሯም በአስፈላጊ ቦታ የሆነ አይደለም። ራሷንም ወደ ኦሮሞ ብሔር ያዘነበለች አድርጎ ያሳያታል።
 
ነገሬ ብላ ፓርቲውን ማሳጣት ላይ ወይም ራሷን እነደሀይለኛ ማስቆጠር ላይ ማተኮሯን የሚያሳይ፣ መሀል ላይ በቃለመጠይቁ ወቅት ያለተጠቀሰ እና ካለደሳለኝ እውቅና የተሰነቀረ የልማታዊ አርሶአደሮች ምስል አለ። በመንግስት የሚደገፈው የአማራ ክልል ቴሌቪዥን (መቼቱ አልተጠቀሰም) ለፕሮፖጋንዳ ያደረገውን ቃለ መጠይቅ እንደማስረጃ መሰንቀሯ ሳያንስ፣ እሱ ተመልክቶት ምላሽ እንዳይሰጥበት ማድረጓ የሙያን ስነምግባር ያጓደለ መሰለኝ።
 
ደሳለኝም ቢሆን “ውሻ በቀደደው ጅብ ይገባል” እንዲሉ፣ እሷ በጀመረችው ማነጻጸር ገብቶ ‘ፓርቲው የተቋቋመው፣ እና የምናደርገውን ሁሉ የምናደርገው ሌሎች ስላደረጉት ነው’ ዓይነት ገደምዳሜ ላይ እንድንደርስ የገፋፋን ይመስላል።
 
የአማራ ፓርቲ ሊቀመንበርነት፣ ፓርቲው ለመደራጀት ገፊ የሆነውን ምክንያት የስሙን ያህል፣ በጥናት እና ንባብ ተደግፎ አጣፍጦ ማስረዳት ይጠበቅበታል/ት ነበር። ቢያንስ ስለፕሮግራም ሲጠየቅ መደናገጥ የሚጠበቅ እና አስፈላጊ አልነበረም። እንጂ፣ ቢያንስ አማራ ኢትዮጵያን በመገንባት ሂደት ያበረከተውን ነገር ለመጥቀስ፣ ስነጥበቡን እና ኪነ ጥበቡን መጥቀስ ብቻውን ይበቃው ነበር።
የእድገት እና የስልጣኔ ጠቋሚ የሆኑትን የወሊድ ቁጥር መቀነስ እና ተያያዥ ዴሞግራፊክ ነገሮችን፣ እንደበደል ማቅረቡም ከምሁርነቱ አይጠበቅም። ከዚያ ይልቅ በቅርቡ እንኳን በአማራ ቴሌቪዥን ላይ የቀረቡትን የእስር ቤት አያያዝ ፕሮግራሞች ጠቅሶ መናገር ይችል ነበር።
 
የአካባቢውን የማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ሁኔታ፣ በጊዜ መዳርን ጨምሮ ሌሎች ልማዳዊ ድርጊቶች ያበረከቱትን አስተዋጾ፣ ት/ት እንዳይስፋፋ እና መሰረተ ልማቶች እንዳይከናወኑ በመደረጉ የደረሱትን ጥፋቶች፣ እንዲሁም ብዙ መውለድ ለመቀንጨር የሚያድርገውን አስተዋጽኦ እና ያም የሚያመጣውን የአእምሮ ውሱንነት ማሰብና፥ ጉዳዩን በተሻለ ማስረጃ ማቅረብ ነበረበት።
 
ወይ ደግሞ እንደ ኢህአዴግ/ብአዴን፥ ፓርቲው ዋና ዒላማ ያደረገው ገበሬውን ሆኖ፣ በአሉሽ አሉሽ እንፍሽፍሽ ማለፍ ፈልገው ይሆናል።
 
በዚህ የተነሳ፣ ማህበረሰቡ ሊደነቅበት በሚገባው ነገር ክስ ማጠናከሪያ አድርጎታል። (ልክ መስታወት ሲሰበር ይቆርጣል፤ ካዩበት ያሳያል እንደማለት ያለ፥ ነገሩን ከብዙ አንግል ማየት እና ትክክለኛ መከራከሪያ ማቅረብ ይቻላል። እኔ እንኳን ከሱ የተሻለ ይህንን ጉዳይ ማስረዳት የምችል ይመስለኛል።)
 
እሷም ጉዳዩ ላይ ንባብ ጠገብ ብትሆን ኖሮ፣ እዚህ ጋር ጥሩ ውይይት ያደርጉ ነበር። ባይሆን ግን የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ሪፖርቶች ላይ የአማራው ቁጥር አንሶ እንዲዘገብ የሚደረግበትን ምክንያት ማህበረ ፖለቲካዊ አድርጎ ማቅረብ እና ነጥብ ማስያዝ ይችል ነበር።
“በአብን ስም ያልተገባ ነገር የሚያደርጉ ስላሉ፣ ግለሰቦች ስለሚጽፉት ነገር ፓርቲው ሊወቀስ አይገባውም” ዓይነት ነገር ባለበት አንደበቱ፣ ስለእነ ግንቦት 7 ሲናገር ርግጠኛ ሆኖ “ደጋፊዎቻቸው” አባባሉም ከወገንተኝነት ያልጸዳ አቋም እንዳለው ነው የሚያሳየው።
 
ደግሞ በአብን ስም ለተደረጉ ስህተቶችስ፣ ፊት ለፊት ቀርቦ የእኛን ፓርቲ አይወክልም ብሎ ወዳጅንም ማረጋጋት፣ ጠላትንም ማስደንገጥ አይቻልም ወይ? ወይስ እንደ ኦነግ ሰው ተገድሎ፣ ሰው ተባሮ “አባላቶቼ አይደሉም። በስሜ ነው ይህን የሚያደርጉት።” ለማለት ነው የሚጠበቀው?
 
ሲመስለኝ፡
 
የአብን ነገር እንደ ትኩስ ሽልጦ “ጠዋት ተመርቶ፣ ከሰዓት መርካቶ” ዓይነት ይመስላል። ምናልባትም ዋና ግብ ያደረጉት ለመጪው ምርጫ መሳተፍ ነው።
 
የምር ለአማራው የሚቆረቆሩ ከሆነ ግን ከሕዝባዊ ስብሰባዎች እና ውይይቶች እኩል፣ ውስጣዊ ውይይቶች፣ የንባብ እና የርስበርስ ስልጠና፣ የመጽሐፍ ተዋውሶ ማንበብ ዝግጅቶችን ማድረግ ይኖርባቸዋል። ያድርጉ አያድርጉ ባላውቅም ከሚናገሯቸው እና ልዩነትን ከሚይዙባቸው ነገሮች ተነስተን፣ ክፍተት እንዳለ በግልጽ መናገር ይቻላል።
ነገሩን ጠቅለል ስናደርገው፡
 
ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ አብንን ሳይወክል፥ ስለአብንም ሆነ አማራ መደራጀት ቢጠየቅ ከዚህ የተሻለ ቃለመጠይቅ ማድረግ ይችል ነበር ብዬ አስባለሁ! ይህም የሚሆነው ከእርጋታ እና ነገሩ ላይ ከመብሰል እንጂ፣ ከግል አቅም አይደለም። ዶ/ር ደሳለኝ እርጋታውን እና ቅንነቱን አሳይቷል።
አብን እንደሶስት ወር ዕድሜው በጣም ጥሩ እየሰራ ነው! እንደ አማራ ሕዝብ ግን ገና ነው! ለሰፊው እና ስልጡኑ አማራ ሕዝብ አብን ይጠበዋል።
 
ባልተያያዘ ወሬ ደግሞ፡
 
እሱ “አብን ለሕብረ ብሔራዊ ድርጅቶች ስጋት ነው” ያላትን ወስጄ፥ ሕብረ ብሔራዊው ግንቦት 7፣ ለአብን ስጋት እንዳይሆን እንደሚፈሩ፤ አባላቱም በዚህም ስጋት የተነሳ ግንቦት7ን ማጥላላት ላይ እንደተጠመዱ ብነግረው አልጠላም።
 
በቅንነት ተደራጁ! የተደራጃችሁም በቅንነት ተራመዱ! በርቱ!
ሰላም!

የምናፍቃቸው ዜናዎች…

06-Bidens macroptera - Adey abeba - 10-Verso Gimma-05-Mascàl-DSC01754
– መንግስት ከሕዝብ የሚሰበስበውን ግብር ገንዘብ አወጣጥ በተመለከተ ግልጽ የሆነ አሰራር መዘርጋቱን አስታወቀ። በዚህም መሰረት በመንግስት ጥሪ ተደርጎላቸው አገር ውስጥ ገብተው ለነበሩ የተቃዋሚ ፓርቲዎች እና ግለሰቦች ይደረግ የነበረው የእለት እና የማረፊያ ወጪ እንዲቋረጥ እና፣ ግለሰቦቹ/ቡድኖቹ ራሳቸውን እንዲያስተዳድሩ ተወሰነ።
 
– ዘር እና ጎጥን መሰረት አድርገው ፓሪዎች እንዳይመሰረቱ፣ ጥብቅ አዋጅ ተላለፈ።
 
– ተቃዋሚ ፓርቲዎች መከባበር የተሞላበት ውይይት አደረጉ። ፓርቲዎቹ በየልሳኖቻቸው ያደረጓቸው ውይይቶች እና ክርክሮችም፣ ፍጹም መከባበር እና ለአገር በሚጠቅም መልኩ መተጋገዝ የታየባቸው ነበሩ።
 
– አድማጭ ተመልካቾቻቸውን ለማስፋት እና ስርጭቶቻቸውን በሰፊው ለማዳረስ በጋራ በነደፉት እቅድ መሰረት፣ ኦኤምኤን እና ኢሳት የ30 ደቂቃ የዜና ሽፋን ሰዓት በቅይይር ተሰጣጡ። በወቅቱ ሚዲያ ከሚዲያ ጋር ተደጋግፎ፣ ሀሳብን የመግለጽ መብትን ለማስረጽ መስራት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ።
 
– አገሪቱ ላይ ባለው የመልካም አስተዳደር ጉድለት እና ፖለቲካዊ እና ወገናዊ ጥቅመኝነት የተቆጡ የአዲስ አበባ ወጣቶች መስቀል አደባባይ ፍጹም ሰላማዊ የሆነ የተቃውሞ ሰልፍ አድርገው፣ እስር እና ወከባ ሳይገጥማቸው በሰላም ወደየቤታቸው ተመለሱ። ፖሊስም ለሰልፉ በሰላም መጠናቀቅ ከፍተኛ ጥበቃ አድርጎ ሕዝባዊነቱን አስመስክሯል።
 
– አገሪቱ ውስጥ እየመጣ ባለው ለውጥ አማካኝነት 3 እስር ቤቶች ተዘግተው ረዳት የሌላቸው አረጋውያን መቆያ ተደረጉ።
 
– በስልጣን ዘመናቸው የሕዝብን ሀብት በመበዝበዝ እና ሰዎች ላይ ኢሰብአዊ ጥቃት በማስፈጸም የተሳተፉ ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው በወንጀለኛ መቅጫ ህጉ መሰረት ቅጣት የተበየነባቸው ሲሆን፣ በወቅቱ ያፈሩት ሀብትም ተወርሶ ለሕዝብ ጥቅም ገቢ ሆኗል።
 
– ሰዎች ሀሳባቸውን ያለገደብ መግለጽ በነበራቸው ፍላጎት የተነሳ፣ በየማህበራዊ ድረ ገጹ ፌስቡክ ላይ የነበረው ትርምስ እና መሰዳደብ በመጥፋቱ፣ ወጣቶች ሀሳብን መሰረት ያደረገ ውይይት ላይ እንዲያተኩሩ እንዳገዛቸው ተናገሩ።
 
– ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት ሁለቱ ብቸኛ ፓርቲዎች በቀጣዩ ምርጫ ላይ ከፍተኛ ፉክክር ያደርጋሉ። ከወዲሁ የምረጡኝ ቅስቀሳቸውን የጀመሩ ሲሆን፣ ምርጫ ቦርድም ለነጻ እና ገለልተኛ ምርጫ ዝግጅቱን ጨርሶ እየጠበቀ ነው።
 
– ጾታዊ ጥቃት እና ትንኮሳ የፈጸሙ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ለተጠቂዎቹ ፍትህ በመሆኑ ደስታ የተሰማቸው ሰዎች ገለጹ።
 
– ኢትዮጵያ ውስጥ በተፈጠረው የስራ እድል እና ሞያን መሰረት ያደረገ ውድድር መሰረት ወደውጭ የሚሰደዱ ምሁራን ቁጥር ቀነሰ። ውጪ የሚገኙ ምሁራንም ወደ አገር ተመልሰው የተለያዩ የስራ መስኮች ላይ እየተሰማሩ ነው።
 
– ህብረት ለእድገት በተባለ የወጣቶች ማህበር ውስጥ ወጣቶች በተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ ተሰማርተው አስተሳሰብን የመቀየር ስራዎችን እየሰሩ ነው። በተለይም አገሪቱ ላይ ለረጅም ዓመታት ተንሰራፍቶ የቆየውን የት/ት እጥረት ለመቅረፍ፣ በክረምት እና በእረፍት ቀናቸው የማስተማር ስራዎችን ያከናውናሉ።
ወዳጄ ጋዜጠኛ ሀብታሙ ስዩም በጋበዘኝ መሰረት፥ የምናፍቀውን ዜና በስስ፣ ድፍርሱ እንዲህ አስፍሬያለሁ። እስኪ ደግሞ የምትናፍቃቸውን ዜናዎች እንድታጋራን ወዳጄ Emebet Lakewን ልጋብዝ።
Join the #mydreamnews campaign