Month: February 2020
“ላሊበላ ቅርስ አይደለም” ከዶ/ር ይርጋ ገላው ጋር ክፍል 2… “የላስታ ገጸ-በረከቶች” (በእውቀቱ ስዩም) | Ethio Teyim | Episode 15
መባቻ (በያሬድ ጌታቸው)
ቢገባን
ዛሬን ስንቀመጥ ፣ ከምቾቱ ወንበር
ትናንትን ባንረሳ ፣ ነገ እንዴት ውብ ነበር!
መንደርደሪያ
ራስን መሆን ከራስ፣ ራስን መሆን ከሌሎች የተውጣጣ ገዢ ሀሳብ አመለካከት አስተሳሰብ እምነት ሊቀዳ ይችላል ። ማንም በራሱ ብቻ ችሎ አይቆምም ወይ በሰው አሊያም በተፈጥሮ ይደገፋል ። ማንም ፍልስፍናውን ከሌለ ነገር ላይ ተመስርቶ አይፈላሰፍም ወይም አያሰላስልም የሌለ ሃሰብ የለም የሌለ ምንለው ካለው ይነሳል ። የኔ የምትለው ሃሰብ ከብዙ በጎነት ወይም ከብዙ ክፋት እየተቀዳ በሕይወት ምልልስ ላይ ደጋግመህ የተለማመድከው ፣ የኖርከው የኖርክለት አስተሳሰባዊ የአንተነት ማንነት ነው ። ራስን ካልቃኙበት መሆንን ያልሆነ መምሰል ልክነት አይደለም ። አይደለም መምሰል ራስን መሆንም ልክነቱ ለራስና ሌሎች በልክነት ለሚመለከቱት ብቻ ነው ። እናም እኔም ራሴን የሆንኩበትን መሻቶቼን የቃተትኩበት ፣ ያሰላሰልኩትን፣ ስሜቴ በሁሉም አውድ የተነካሁበትንና ምናቤ በነጎደበተን መንገድ ተከትዬ ለእኔ መጀመሪያ ለእናንተ ደግሞ ስጦታ በሆነችው “መባቻ” የበኩር ስራዬ ራስን በመሆን ውስጥ ራስን መግለጥ ባተ ፡፡