መባቻ (በያሬድ ጌታቸው)

                ቢገባን
ዛሬን ስንቀመጥ ፣ ከምቾቱ ወንበር
ትናንትን ባንረሳ ፣ ነገ እንዴት ውብ ነበር!

መንደርደሪያ85091577_2528096727454843_9219331980162760704_n

ራስን መሆን ከራስ፣ ራስን መሆን ከሌሎች የተውጣጣ ገዢ ሀሳብ አመለካከት አስተሳሰብ እምነት ሊቀዳ ይችላል ። ማንም በራሱ ብቻ ችሎ አይቆምም ወይ በሰው አሊያም በተፈጥሮ ይደገፋል ። ማንም ፍልስፍናውን ከሌለ ነገር ላይ ተመስርቶ አይፈላሰፍም ወይም አያሰላስልም የሌለ ሃሰብ የለም የሌለ ምንለው ካለው ይነሳል ። የኔ የምትለው ሃሰብ ከብዙ በጎነት ወይም ከብዙ ክፋት እየተቀዳ በሕይወት ምልልስ ላይ ደጋግመህ የተለማመድከው ፣ የኖርከው የኖርክለት አስተሳሰባዊ የአንተነት ማንነት ነው ። ራስን ካልቃኙበት መሆንን ያልሆነ መምሰል ልክነት አይደለም ። አይደለም መምሰል ራስን መሆንም ልክነቱ ለራስና ሌሎች በልክነት ለሚመለከቱት ብቻ ነው ። እናም እኔም ራሴን የሆንኩበትን መሻቶቼን የቃተትኩበት ፣ ያሰላሰልኩትን፣ ስሜቴ በሁሉም አውድ የተነካሁበትንና ምናቤ በነጎደበተን መንገድ ተከትዬ ለእኔ መጀመሪያ ለእናንተ ደግሞ ስጦታ በሆነችው “መባቻ” የበኩር ስራዬ ራስን በመሆን ውስጥ ራስን መግለጥ ባተ ፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s