አንድ ዕድል ሰጥተሽኝ ልካስሽ ደግሜ፣
ያውም አገልጋይሽ ታማኝ ባሪያሽ ሆኜ
ያልጠፋነው፣
ከእግዚአብሔር ምህረት የተንሳ ነው”ን
አንድ ዕድል ሰጥተሽኝ ልካስሽ ደግሜ፣
ያውም አገልጋይሽ ታማኝ ባሪያሽ ሆኜ
ያልጠፋነው፣
ከእግዚአብሔር ምህረት የተንሳ ነው”ን
“ኀዘንሽ ቅጥ አጣ
ከቤትሽ አልወጣ፤
ገደለው ባልሽ፤
የሞተው ወንድምሽ!”
ኮካው ማረኝ ማረኝ
ኮካው ማረኝ ማረኝ
የዘንድሮስ ካድሬ ጭራሽ አላማረኝ
አገሩ ከደረ፣
መንደሩ ከደረ
አበል መክፈል ቀረ
“እንደምን ነሽ ሸገር
የእነ ሮቤል ኪሮስ፣ የኮካዎች አገር”
ካለነገር አይደለም ሮቤልን (aka the whale) ጠቅሼ ነገሬን መጀመሬ። ስለስፖርት እና ስለዓለም አቀፍ ውድድሮች ውክልና ሲወራ፥ ያለውን የተበላሸ አሰራር መልክ በሱ ልክ ለዓለም ያሳየ የለምና ነው። ያው ኮካ ኮካ ነው። ድራሹ ይጥፋ!
ሰበቤ ደግሞ ፈረንሳይ ውስጥ በምትኖርበት አፓርትመንት ውስጥ በኤርትራዊ ወጣት በትራስ ታፍና፣ በተሸለመችው ዋንጫ ጭንቅላቷን ተመትታ የሞተችው የ27 ዓመቷ ኢትዮጵያዊት ዝናሽ ገዝሙ ናት። ሞቷ/አሟሟቷ እጅግ በጣም ያንገበግባል። 😥 ነፍሷን ይማረው! ለቤተሰቦቿም መጽናናት ይኹን!
ግን ለምን ተሰደደች?? እሷ ብቻ ሳትሆንም ብዙ አትሌቶች ለምን ተሰደዱ/ይሰደዳሉ? አሸንፈው በቴሌቪዥን እስኪታዩ ድረስስ እንዲህ ባለ ውጣ ውረድ ውስጥ እንደሚያልፉ ስንቶቻችን አስበነው እናውቃለን? አገር ውስጥም በሶ መበጥበጫ ካቅሙ ብርቅ ሆኖባቸው በታጠፈ አንጀት ልምምድ የሚያደርጉ ስንት ተስፈኛ ወጣቶች አሉ!? እንደዜጋ ቢቀር፥ መንግስት እንደ ኢንቨስትመንት ቆጥሮት፥ ከድሀው ሕዝብ የተሰበሰበውን፣ ከገደላ ገደሉ ቀፈቴ ቆንጥሬ እንዴት “ቀለብ ልስፈርላቸው” አይልም?
(ሌላ ሞያ ላይ ያሉትን ዜጎች ትቼ ስለአትሌቶቹ መጠየቄ፥ ዕድሉን ካገኙ፣ የልፋታቸው ውጤት የትም ተሁኖ በንጹህ ላብ የተጠራቀመ ጠቀም ያለ ገንዘብ፣ ክብርና ዝና መሆኑ ስለሚታወቅ ነው። እንዲህ ያሉ ለሀገር ሀብትም፣ ክብርም መሆን የሚችሉ ብርቅዬዎች፥ የውጭው በር የሚከፈትላቸው የውስጡ በር እንዴት እንዴት ተዘግቶባቸው ውጭ ውጭ ቢያሳያቸው ይሆን? ብዬ ነው።)
በርግጥ እንደ ፈይሳ ሌሊሳ ያሉ ግልጽ በሆነ ፖለቲካዊ አመለካከታቸው የተነሳ የሚሰደዱ አሉ። አብዛኞቹ ግን ችሎታ እያላቸው፥ ዘመድ ስለሌላቸው ውድድሮች ላይ የመሳተፍ በሮች እየተዘጉባቸው እንደሆነ ይፋዊ በሆነ መልኩ ባይሆንም በገደምዳሜ ይሰማል። ሯጮቹ ገጽታ ላይም የሚታይበት አጋጣሚ ብዙ ነው። በተለይ ውድድሮችን አሸንፈው ለሽልማት ሲበቁ የሚጎርፈው እንባቸው ዝም ብሎ የደስታ ብቻ አይመስለኝም።
ከጀርባ የነበረው መገፋት እና ትግል፣ ልፋትና ጥረት ሁሉ ተደራርቦ ድል ማድረግ እንደ ደራሽ ወንዝ የሚፈጥረውና፣ ቁጭት የሚያባብሰው ይመስለኛል። (የመሰረትን የለንደን ኦሎምፒክ ዕንባ ያስታውሷል።) ከጥረታቸውና ልፋታቸው ጎን ለጎን ደራርቱና እልፍነሽ ቀድመው ከቤተሰቡ ባይኖሩ ኖሮ ገንዘቤ እና ጥሩነሽን የመሰሉ ብርቆች ላናውቃቸው፣ ወይም ደግሞ ተሰደው የሰው አገር ጌጦች ሆነው ልናውቃቸው… በነሱ ምትክ ደግሞ ቦርጫም ሯጮች ልናይ እንችል እንደነበር አስበነው እናውቃለን?
ግን ዝናሽ ለምን ተሰደደች??
ዝናሽ በዋናነት፥ ለመኖር እና፣ ወላጅ እናቷን ለመጦር ተስፋ ያደረገችው አትሌቲክሱን እንደነበርና፥ የአትሌቲክስ ልምምዷን ላለማቋረጥ እና፣ እሳቸውንም ለመደገፍ በሳምንት እስከ 270 ዶላር ድረስ የምታገኝበትን ሆቴል የማጽዳት ሥራ እየሰራች፣ ከሌሊቱ 11 ሰዓት እየተነሳች ሥራ ከመሄዷ ቀድማ፣ እንዲሁም ምሽት ከሥራ ስትመለስ ጧትና ማታ ልምምድ ታደርግ እንደነበርና፥ ይኽ ጥረቷ እና ጥንካሬዋም ቡድኗ ውስጥ ከነበሩ በርካታ አትሌቶች ለየት እንደሚያደርጋት ጠቅሶ ስለልዩ ጥንካሬዋ የቀድሞ አሰልጣኟ ኒኮላስ ቫላት ተናግሯል።
አትሌት ኃይሌ ገ/ሥላሴ በጀርመን ድምጽ ሬድዮ ላይ በሙስና እና የዘመድ አሰራር ዙሪያ ተጠይቆ ሲናገር “የዝምድናው፣ የሙስናው፣ የመሳሰሉት በየትም ቦታ አሉ፤ ግን ልዩ የሚያደርገው በስፖርቱ የምታየው ሙስና እና የዝምድና የመሳሰሉት ነገር ሜዳ ላይ ቁልጭ ብሎ ለሚሊዮኖች ይታያል። ያ ደግሞ ያጋልጥኻል ማለት ነው። ምንም የፖሊስ ምርመራ ሳያስፈልገው የሚጋለጥ ነገር ነው። እኔ የምጥረው ያ እንዳይኾን ነው።” ማለቱም ይታወሳል።
እንግዲህ እሱ ከውስጥ ሆኖ በዚህ ደረጃ ከገለጸው፥ በውጭ ያለነው ሰዎች ስለአትሌቶች ስደት ሲወራ፣ እንደ ዋና ምክንያት የአሰራሩ ብልሹነት ነው ብንል ልክ አይደላችሁም አንባልም ማለት ነው።
ሆኖም “ሞተች” የተባለችን ምስኪን “ለምን ተሰደደች?” ብሎ መጠየቁ፥ ሌሎች የሞያ አጋርና እኩዮቿ እንዲጠበቁ ጥሪም ጭምር ነውና፥ በእሷ ሞት የተነሳ አንድ እንኳን ተስፋ ያለው አትሌት፣ አገሩ ላይ ተለማምዶ አገሩን ወክሎ መወዳደር እየፈለገና እየቻለ፥ ባለጊዜ ካለመሆን የተነሳ ብቻ ዕድል እንዳይነፈገው ቢቻል፣ ለከርታታ ነፍሷም ጥሩ እረፍት ይሆን ይመስለኛል። መታሰቢያዋም ሁሌ ይኖራል።
.
.
ከልፋቷ ለማረፍ ላይ ታች ስትል መቀጨቷ ያሳዝናል። እግዚአብሔር ነፍሷን ይማረው። ለቤተሰቦቿም መጽናናት ይስጥ። አገዳደሏም በጣም ያሳዝናል። ገዳይዋም ተገቢውን ፍርድ እንደሚያገኝ እናምናለን። ዝናሽ በዋናነት የማራቶን ሯጭ ብትሆንም፥ በ10ሺ፣ ግማሽ ማራቶን እና ሌሎች የቤት ውስጥ ውድድሮች ፈረንሳይ ውስጥ ብዙ ጊዜ ማሸነፏ ተገልጿል።
ነፍሷ በሰላም ትረፍ!
❤
ጋሽ ስብሀትን አንድ ጋዜጠኛ
“ከቅርብ ጊዜ ዘፋኞች የምትወደው” ሲለው
“ይኼ ነይልኝ…የሚለው ልጅ ይመቸኛል“
ጋዜጠኛው ቀጠል አድርጎ
“የማይመችህስ ዘፋኝ?” ሲለው
“ከእሱ እየተቀበለ “ነይለት” የሚለው አቃጣሪ” አለው አሉ።
ይኼን ያስታወስኩት ዮሴፍ ገብሬ (ጆሲ) እና ያ ቀልማዳ ልደቱ አያሌው ያወሩትን ዞር ዞር ብዬ ተመልክቼው፥ አንዴ ጆሲን፣ አንዴ ልደቱን እያልኩ መመዘኑ ሰለቸኝና ነው።
ቃለ መጠይቁ ሲጀምር እና “የፍቅር እስከ መቃብር ደራሲ ማነው?” በሚል ጥያቄ ነው። ተመልካቾች በ2 ብር (?) የጽሁፍ መልእክት ሰዎች ምላሽ እንዲሰጡና፣ ከመካከላቸው አንዱ ስጦታ እንደሚበረከትለት ይገልጻል። ማስታወቂያው በየመሀሉም ለብዙ ጊዜ ይደጋገማል። የመጀመሪያው መላሽ ለሚሸለም ያን ያህል መደጋገሙስ ለምን አስፈለገ? ማለቴ አልቀረም። በሁለተኛው ክፍል ደግሞ ጥያቄው “ይኽች አርቲስት ማን ትባላለች” ብሎ የእንግዳዘርን ምስል ነው የሚያሳየው።
ብቻ ሕዝቤ በነፍስ ወከፍ ሁለት ሁለት ብሯን አዋጥታ ታበረክታለች። ይመቻቸው!
የመጽሐፍ ነገር ሲነሳ፥ የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ሳለው መምህሬ የነበረና፣ አሁን የቅርብ ወዳጄና አማካሪዬ ጋር ከሳምንታት በፊት ስናወራ በጨዋታ መሀል ያነሳብኝ ነገር ትዝ አለኝ።
ከወዳጄ ጋር የነበረን ጨዋታ፥ እንደአገር ስላለመታደላችን፣ ይኽ ነገር የሚቆምበት ጊዜ እንደሚናፍቀን፣ እንዲሁም ድርሻችንን ለመወጣት በየዙሪያችን ራስን ከመለወጥ አንስቶ መሞከር እንጂ፥ የሚታይ የሚሰማው ነገር ሁሉ ተስፋ አስቆራጭ ስለመሆኑ ነበር። ነገርን ነገር አንስቶት ወዳጄ ጆሲን አስታወሰው።
“በጣም ነው የሚያሳዝነው። የሚዲያ ባለቤት እንኳን ለእፍረት ብሎ ስለንባብ የሚገነባ ነገር አያወራም።
አሁን ባለፈው ጆሲ የሚሉት ልጅ ከአንድ ሌላ ጋዜጠኛ ጋር ያወራል። ጋዜጠኛው “መጽሐፍ ታነባለህ ወይ?” ብሎ ይጠይቀዋል።
“አሁን አላነብም። ድሮ ግን አነብ ነበር።” አለው ኮራ ብሎ።
“እስኪ ድሮ ካነበብካቸው መጽሐፍት ያንዱን ርዕስ ንገረን” ሲለው፥
“አሁን ትዝ አይለኝም።” አለው።
ምናለ የአንዱን መጽሐፍ ርዕስ እንኳን ቢጠራ? ቢቀር ፍቅር እስከ መቃብር አይልም ሰው? እንግዲህ ይኽ የሚዲያ ባለቤት፣ ጋዜጠኛ እና ዘፋኝ ነኝ የሚል ሰው ነው። ሌላውን ደግሞ አስበው።” ተባባለን፣ መዓዛ ብሩን አወድሰን አለፍን። (ባይጠቅመኝም ሌላ ቃለ መጠይቁን የሰማ፥ ወይ ከማን ጋ እንደሆነ የሚያስታውስ ካለ ቢነግረኝ እና ብሰማው ደስ ይለኛል።)
መዓዛ ብሩን ስናወሳ ስለእንግዶቿ ያላትን ጥልቅ እውቀት እና፣ ስለሰሩት ነገር ለማወቅ ጥናት/ምርምር ስለማድረጓም ጭምር ነው።
ይኽን ማንሳቴ ደግሞ ጆሲ ስለእንግዳው እንዴት ጥናት አያደርግም? ቢያንስ ከጻፋቸው መጽሐፍት አንዱን በወፍ በረር ቃኝቶ ማውራት ቢቀር፥ እንዴት ስለመጽሐፎቹ እሱ እንዲናገር እንኳን የመጽሐፉን ወሬ አያነሳበትም?
ጭራሽ ስለመጽሐፍና ንባብ፣ ስለጻፈው ልብወለድ ሲያነሳበት ሁሉ፥ የጆሲ ልብ ፔጆዋ ላይ ነው ጆፌ ብላ የቀረችው።
ብቻ ያው ነው።
ጆሲ “ሰማሁ… አሉ…”
ልደቱ “አልኩ… አደረግኩ… እኔ መሲሁ ነኝ። ልወደድ አልልም። ሕዝቡ ይወደዋል አይወደውም አልልም። እኔ ካመንኩበት እናገረዋለሁ።”
ያው መበጣረቅ ነው!
ሕዝብ ካልወደደው ለአገር ምኑን ጠቀመ? “አገር ማለት ሰው ነው” እንደሚባል አያውቅም ማለት ነው? ለነገሩ፥ ቤቴ ውስጥ ይሉኝታ ያጠቃኛል። በፖለቲካ ግን ይሉኝታ አላውቅም ብሎ ነገሩን ሲጀምር ነበር ማቆም የነበረብኝ።
የተቸገርነው እኮ አገሪቱን እንደቤታቸው አላከብር እያሉን ነው። ሕዝቡን እንደወገናቸው አልቆጥር እያሉን ነው።
ይኽን ስጽፍ ፌስቡክ “የዛሬ ዓመት ምን ብለህ ነበር” ቢለኝ ጥሩ ነው?
እንደው… የሞት የሽረት “ግድ መምረጥ አለብህ” ብባል፥ አይደለም ከሌላ ሌላው…
“መለስ ዜናዊ ከልደቱ አያሌው ብዙ ጊዜ ይሻለኛል!” እላለሁ! Period! ብለህ ነበር ይለኛል።
ምድረ አተቲያም፥ “የአረም እርሻ” ገበሬ! ጆሲን ግን ጥሩ ለጎም ለጎም፣ ጎተት ጎተት አድርጓታል። ሃሃሃ…
እኔማ ከ1992 ዓ/ም (ለመጀመሪያ ጊዜ ቲቪ ላይ ካየሁት ጊዜ) “ሆኜ፣ ተደርጌ” ሲል ሰምቼው እንደቀፈፈኝና ቀልማዳነቱ ብቻ እንደሚታየኝ አለ። He is one of the persons/things that time and time prove my instinct right.
ሃሌሉያ!