ፈተናዎች…

የዛሬ 8 ዓመት ገደማ፥ በወርሀ ሰኔ፣ “ገሳ ልልበስ፣ መሬት ልረስ” በማይባልበት የሀዋሳ ከተማ፣ ከሞኝ አበስብስ ዝናብ ጋር ተሯሩጬ፥ አልፎ አልፎ፣ ከመደበኛ የቢሮ ሰዓት በኋላ፣ ከጥቂት ወዳጆች ጋር ተሰብስበን የበጎ ፈቃድ ሥራ የምናግዝበት፥ በቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሥር በተቋቋመ የምግባረ ሠናይ ኮሚቴ ቢሮ ውስጥ ገባሁ።
 
በወጨፎ የቆሸሸ ሱሪዬን ማራገፍ፣ በዝናብ የራሰ ፀጉሬን መጠራረግ እንደጀመርኩ አንዲት ህጻን እያለቀሰች ገባች። ሹራቡ የተተለተለ ዩኒፎርም ለብሳለች። በዝናብ የረጠቡ ደብተሮች በቀኝ እጇ ከደረቷ ጋር አጣብቃ ይዛ፣ ከእንባዋ ጋር ተቀላቅሎ ሊወርድ የሚለውን ንፍጧን ሳብ እያደረገች ታለቅሳለች። ከተማው ውስጥ ካሉ ቤቶች የነጻ ትምህርት ፈቃድ አግኝተን፣ ቁርስ (አምባሻ በሻይ) እዚያው ግቢ ውስጥ ተመግበው፣ ለምሳ ሽሮ ተቋጥሮላቸው ትምህርት ቤት እንዲሄዱ ከምናግዛቸው 45 የተማሪዎች መሀል አንዷ ነበረች።
 
[…ተማሪዎቹ ጎዳና ላይ ያለፈ ያገደመውን ለምነው (ሲችሉም አምታተው) የሚኖሩ ወላጅ አልባዎች፣ ወይም ከወላጆቻቸው ጋር ተጋግዘው በልመና የሚተዳደሩ ናቸው። በወቅቱ የኮሚቴው አቅም ቁርስና ምሳ ማብላት ብቻ ስለነበር፥ ከትምህርት ቤት ሲመለሱ አማራጭ በማጣት ወደልመናው ያቀናሉ። ከዚህም ባሻገር፥ ወላጆቻቸው ት/ቤት ሲሄዱባቸው የገቢ እጥረት ስለሚያጋጥማቸው፣ ልጆቹ ትምህርት እንዲያቋርጡ እንቅፋት ይሆኑባቸዋል።
 
የእኛ ዋና ሥራ፥ የማይጠቀሟቸውን አልባሳት እና ወርሃዊ መዋጮ የሚያደርጉ አባላትን ማስተባበር፣ ለዕለት ዕለት ምግብ ማብሰያ የሚወጣውን ወጪ መጠየቅ፣ እንደ ዩኒፎርም እና ደብተር የመሳሰሉ ዓመታዊ ቁሶችን ጊዜያቸው ሲደርስ ማሟላት፣ እና ህጻናቱ ወገንተኝነት እንዲሰማቸው፣ በትምህርትም እንዳይዘናጉ ‘አለሁ’ የማለት ያህል ነበር። ለምግብ ሥራው የተቀጠረ ሰራተኛ ነበር። ከበጎ አድራጊ በተገኘ የቆርቆሮ እና የሰራተኛ ክፍያ ድጋፍም ኩሽና እና ለመመገቢያ መጠለያ እንዲሆን እንደነገሩ ተመቷል። ሥራው መንፈስን ቢያጽናናም፣ በውስጡ መፈጠርን የሚያስመኙ ብዙ ፈተናዎች ነበሩት…]
 
በትምህርቷም ምስጉን ሆና፥ ለሽልማት የወላጆች ቀን ጥሪ ሁላ መጥቶልን ያውቃል።
 
“ምን ሆነሽ ነው?” አልኳት፥ ‘ይህኔ አንዱ ጥጋበኛ ሰካራም መቷት ይሆናል’ ብዬ ግምቴን አስቀድሜ።
 
የሹራቧን እጅጌ ሰብስባ በመዳፏ ይዛ፣ በአይበሉባዋ ዐይኗን እየጠረገች “ደብተሬን ዝናብ አጠበው” ብላኝ እሪታዋን እንዳዲስ አቀለጠችው።
 
“አይዞሽ በቃ፣ ሌላ ደብተር እሰጥሽና ትገለብጪያለሽ” አልኳት።
 
“ፈተና ደርሷል። ገልብጬ አልደርስም።” ብላ እዬዬዋን ቀጠለች። ምን ይደረጋል?
 
በሌላ ጊዜ እንዲሁ አንድ ልጅ እያለቀሰ መጣ። እናት የሞተችበት ያህል ነው የሚያለቅሰው። “ምን ሆነህ ነው?” ሲባል፥
 
“አባቴ ዩኒፎርሜን ሸጦ ጠጅ ጠጣበት” አለን።
 
እንዲህ ያሉ ብዙ ዓይነት ፈተናዎች ነበሩ።
 
ዩኒፎርሙን ደብቃ፥ “ጠፋብኝ ብለህ ተቀበል” ብላ የላከችም እናት ገጥማን ታውቃለች። ተስፋ ማየታቸው ሲታይ ግን ለራስም ትልቅ ተስፋ ይሰጥ ነበር።
 
18601528_1723104617701544_1109331304_nይሄ ትዝ ያለኝ፥ ሰሞኑን በVOA Amharic በኩል ከወደ ሀረርጌ የሰማነውን የመምህር ተስፋ አለባቸውን 40 ልጆችን ከጎዳና አንስቶ፣ ከሆቴል በተራረፈ ምግብ ወደ ትምህርት ቤት የመላኩ ቢያስደንቀኝ ነው። ልጆቹ የተረጂነት ስሜት እንዲያድርባቸው የማይፈልገው ተስፋ፥ የጠየቀው ነገር፣ ለልጆቹ ቋሚ ገቢ ማግኛ እንዲሆን የእንጀራ መጋገሪያ ምጣዶች እና የልብስ ማጠቢያ ማሽኖች እንዲገዙለት ነው። ከ4 ቀናት በፊትም፥ ከሌሎች ወዳጆች ጋር ሆነን የጠየቀውን ገንዘብ እና ተጨማሪ የ6 ወር ወጪ ይሆናል ያልነውን ለማሰባሰብ የgofundme ገጽ (https://www.gofundme.com/40-dreams-40-hopes-one-donation) ተከፍቶ ይህ ጽሁፍ እስከተለጠፈበት ጊዜ ድረስ፣ በ65 ሰዎች መዋጮ $3,590 ማግኘት ተችሏል። (ሊንኩን ተከትለው ሙሉ ታሪኩን ያንብቡ።)
 
ዕቅዱን ለማሳካት የቀረው እንዲሟላ፣ የምትችሉ ከ$5 ጀምሮ በማዋጣት ልጆቹን “አይዟችሁ፣ በርቱ” እንበላቸው። ያልቻላችሁ፣ በማትችሉበት ሁኔታ ያላችሁ ደግሞ፥ መልእክቱን SHARE ብታደርጉት፣ ሌላ አቅምና ሁኔታ የሚፈቅድለት ሰው አይቶት እንዲያግዝ ምክንያት ትሆኑታላችሁና፥ አደራ!

አሰፋ ጫቦ ተገደለ ወይስ ሞተ?

ቬሮኒካ መላኩ 18119501_10212516554410253_4349511308389670468_n

ባለፈው ወር አካባቢ የቦርከና ድረ ገፅ ባለቤት የእለት ስራውን እያከናወነ እያለ ከሌላኛው የአለም ጫፍ ከወደ አውስትራሊያ አንድ አጠር ያለች መልእክት ትደርሰዋለች ። ይች መልእክት ቦርከና የመልእክት ሳጥን ውስጥ በገባችበት ሰአት በሌላኛው የአለም ጫፍ አንድ በሙሉ ጤንነት ላይ የሚገኝ ሰው ዳላስ ውስጥ ምናልባት ራሱ ያፈላውን ቡና ከሲጃራው ጋር እያወራረደ ይሆናል ወይም ደሞ ብዙውን ጊዜውን የሚያዘወትርበት ቤተ መፅሃፍት ቤት ውስጥ ይሆናል ። ሁለቱንም ልማዶቹን በጣም ይወዳቸዋል ። ይህ ሰው በሙሉ ጤንነት ይገኝ የነበረው አሰፋ ጫቦ ነበር ።

መልእክቷ ምን ትላለች?

የቦርከናው ድረ ገፅ ባለቤት መልእክቷን ሲከፍታት እንደዚህ ትላለች

” ሰላም ጠና ይስጥልኝ ። ስሜ ግሪጎሪ ማኬንዚ ይባላል ። አቶ አሰፋ ጫቦ ጋር እንተዋወቃለን ። ሁለታችንም በዓለም በቃኝ እስር ቤት ጓደኛ ነበርን ። እባክህ የአቶ አሰፋ ጫቦን የኢሜይል አድራሻ ላክልኝ። ከምኖርበት አውስትራሊያ ወደ አሜሪካ ስለምጓዝ አሰፋን ማግኘት እፈልጋለሁኝ ። ሁለታችንም ስላረጀን የመጨረሻ እድሌ ሊሆን ይችላል ። ” ይላል

ይች አጭር መልእክት የደረሰችው የቦርከናው ድሜጥሮስ ብርቁ ወድያውኑ ለአቶ አሰፋ በፌስ ቡክ ሜሴጂ በኩል የሚከተለውን መልእክት ይልካል :

” ጋሼ አሰፋ ሰላም ነዎት ወይ? አንድ ግሪጎሪ ማኬንዚ የሚባል ሰው ከወደ አውስትሪሊያ ኢሜሎትን ጠየቀኝ ። ሰውየው በአለም በቃኝ እስር ቤት አብረን አሳልፈናል እያለ ነው ። ጓደኛየ ነበሩ ብሏል ። ግለሰቡን ያውቁታል ወይ ? ” በማለት ይፅፍላቸዋል ።

አሰፋ ጫቦም ስሙን በማስታወስ ” አዎን ! በማእከላዊ እስር ቤት ካገኘኋቸው አዋቂ የምላቸው ሰዎች አንዱ ነው ፤ ኢሜይሌን ስጠው ” ብለው መለሱ።

የአቶ አሰፋን መልስ ያገኘው የቦርከናው ድረ ገፅ ባለቤት አቶ አሰፋ የሰጡትን የኢሜይል አድራሻ ለግሪጎሪ ማኬንዚ ይልክለታል ።
ከቀናት በኋላም አቶ አሰፋ ወደ ቦርከና በላኩት መልእክት ” ግሪጎሪ ማኬንዚ በስልክ እንዳገኛቸው እና ወደ አሜሪካ ሲመጣ ዳላስ ቴክሳስ ለመገናኘት እንደተቀጣጠሩ ይነግሩትና ። ” ምስጋና ጨምረው ይፅፉለታል ።

ቀድሞ በተያዘው ቀጠሮ መሰረት አቶ አሰፋ ጫቦ እና “ሊጎበኛቸው” ዳላስ ድረስ የሄደው ግሪጎር ማኬንዚ ማርች 27 ቀን ዳላስ (ዳውን ታውን) ተገናኙ። በወቅቱ ሁለቱ ግለሰቦች ሲገናኙ አቶ አሰፋ ጫቦ ምንም አይነት የህመምም ሆነ የድካም ምልክት ያልነበራቸው እና እንዲያውም ለእድሜያቸው በጣም ጠንካራ የሚባል ሁኔታ ላይ እንደነበሩ ነበሩ ።
ይሄንም የሚያረጋግጥ ምናልባት ከራት ሰዓት በፊት በሚመስል ሁኔታ አብረው የተነሱትንም ፎቶ ግራፍ አለ።
ሶስት ሰዓት በዘለቀው ቆይታቸው ፤ በእራት ሰዓት በአንድ የጣሊያን ሬስቶራንት ራት በልተው ፤ እንደገና ለመገናኘት ቀጠሮ ይዘው ተለያዮ።

በማግስቱ አቶ አሰፋ ጨቦ ታመው ሆስፒታል ሄዱ። አቶ አሰፋ ጫቦ የመጨረሻዋን ኤሜይል ለግሪጎሪ ፃፉ “በምግብ መመረዝ” ። እንደታመሙ እና ስለህመማቸው ስሜት በዝርዝር ከፃፉለት በኋላ ዳግም ሊያገኙት ያልቻሉበትን ምክንያት ሆስፒታል መግባታቸው እንደሆነ ገለፁለት ። ”

ከአውስትሪሊያ ወደ አሜሪካ አቶ አሰፋን ጫቦን ለማግኘት ብዙ ሺህዎች ማይል አቋርጦ ዳላስ የደረሰውና አብሮአቸው ራት የበላው ግሪጎር ማኬንዚ ምንም የሆነው ነገር የለም።
ከዚያ በኋላ አቶ አሰፋ ከሆስፒታል አልተመለሱም። የግሪጎሪ ማኬንዚን እራት ተከትሎ ወደ ሆስፒታል የገቡት አቶ አሰፋ ከሆስፒታሉ ድነው ሳይሆን የወጡት ህይወታቸው አልፎ ነበር ።
እንቆቅልሹ የሚጀምረው እዚህ ላይ ነው ።

ለአለፉት 40 አመታት አቶ አሰፋ ጫቦ ከተለያዩ የፖለቲካ ሃይሎች ጋር ግልፅና ስውር ሽኩቻ ሲያደርግ ቆይቷል ። ዋጋም ከፍሎበታል ። ኢትዮጵያ ውስጥ እና በአካባቢው ያሉ የፖለቲካ ሃይሎች ወያኔ ፣ ኦነግ ፣ሸአቢያ ፣ ኢህአፓ እና መኢሶኖች አሰፋ ጫቦ ላይ ብዙ ክሶችን ፅፈውበታል ። እሱም የሚያውቀውን የድርጅቶችን ገበና ሳያቅማማ ሲፅፍ ነበር ። እነዚህ ፓርቲዎች በግለሰብ ደረጃ እንደ አሰፋ ጫቦ በእጅጉ የሚፈሩት አልነበረም፡፡ የሸአቢያን ፣ የወያኔንና የኦነግን ሴራ የሚያጋልጠው ፅሁፉ ፅፎ ካሰራጨና በመላው አለም መነጋገሪያ ከሆነ እንኳን ሁለት ወር አይሞላውም ነበር ።
አሰፋ ጫቦ በብሩህ አዕምሮውና በላቀ የእውቀት ደረጃው ብዙዎቹን ፖለቲከኞች በእጥፍ ድርቡ ያስከነዳቸው ነበር ፡፡ በዚህ የተነሳም አሰፋ ጫቦን ለአመታት ሲሰሩት የነበረውን ድብቅ ሴራ አውጥቶብናል ገና ወደፊትም ያወጣብናል እያሉ አጥብቀው ይፈሩትና አምርረው ይጠሉት ነበር ።

አሰፋ ጫቦ ጠንቃቃና የማስታወስ ችሎታ የነበረው አዛውንት ስለነበር በኢትዮጵያ ውስጥ እና በኢትዮጵያ ላይ የተሰሩ የድብቅ ሴራዎችን በጥንቃቄ ይዟቸው ኖሮ እያወጣ መጎልጎል ጀመረ ። በመለስ ዜናዊ የውሸት ክስ ሀገር የተባረረው አሰፋ ጫቦ በአሜሪካ አገር በስደት መኖር ጀመረ፡፡ የተለያዩ የፖለቲካ ሃይሎች ግን በብዙ ሺ ኪሎ ሜትሮች ርቆ በሰው ሀገር የሚኖር ቢሆንም የአሰፋ ጫቦ ነገር እንቅልፍ ሊሰጣቸው እንዳልቻለ ብዙ ጠቋሚ ምክንያቶች ነበሩ ።፡ አቶ አሰፋ ጫቦ በተለያዬ ጊዜ በሚፅፋቸውና በሚያጋልጣቸው ድብቅ ሴራዎች “የቀን ቅዠት ሆኖ እያባነነና እያስበረገጋቸው እንደነበር ይታወቃል። ሌሎቹንም የተደበቁ ሴራዎች እየፃፈ እንደነበር ተናግሯል ።

የአቶ አሰፋ ጫቦ የማስታወሻ ደብተር ብዙ ጉዳዮችን አጭቂ የያዘ እንደነበር መገመት አይከብድም ። የኢትዮጵያ ፖለቲካ
እንደ ቆሰለ ጅብ የመበላላት አባዜ የተጠናወተው ነው ። ሸፍጡን እና ሴራውን ለመደበቅ አንዱን ገድሎ ስልጣኑን ማደላደል የተለመደ ነው ። ይሄ ለአመታት የተለመደ መርዘኛ ሂደቱን ቀጥሏል ። ከአንድ ሰሞን ከንፈር መምጠጥ ባለፈ “ ይሄ ሰው እንደት ሞተ? “ለምን ተገደለ?” በማን ተገደለ? ገዳዩ ለፍርድ ይቅረብ ወዘተ” የሚል ባህል የለንም ።

የአሰፋ ጫቦ ጉዳይ ገዳይ ተገዳይ ድራማ ያለበት መስሎ ይሰማኛል ፡፡ በዚህ የገዳይ ተገዳይ ድራማ ውስጥ ብዙ ተሳታፊዎችን መጥቀስ ይቻላል ። አሰፋ ጫቦ በብእሩ ጫፍ ያቆሰላቸው ብዙ ናቸው ። “የትዝታ ፈለግ ” በሚለው መፅሃፉ CIA ኢትዮጵያን ለማፍረስ ሱዳን ካርቱም ላይ መሰርቶት የነበረውን ጣቢያ አጋልጧል ።

“የተሰነይ ጉባኤ ” በሚለው ፅሁፉ ወያኔ ፣ሸአቢያ እና ኦነግ በኢትዮጵያ ላይ የሰሩትን ሴራ ለህዝቡ አሳውቋል ። ለወደፊቱም የሚያጋልጣቸው ብዙ ሚስጥሮች እንዳሉት እና እያዘጋጃቸው እንደነበር ነግሮናል ።

ስታሊን ከአባት ሀገር ያባረረውን ሊዮን ትሮትስኪ በብዙ ሺ ኪሎ ሜትሮች ርቆ በሰው ሀገር ሜክሲኮ የሚኖር ቢሆንም የሊዮን ትሮትስኪ ነገር እንቅልፍ ሊሰጠው ስላልቻለ በመጥረቢያ አስፈልጦ አስገደለው ። ወያኔ በኬኒያ እና በሱዳን የሚኖሩ ተራ ስደተኞች እረፍት ሲነሷት ወደ አገሮቹ ጎራ በማለት እንደምትገድል ይታወቃል ። CIA ም ቢሆን ጠላቴ ትንሽ ነው ብሎ አይንቅም ። ኦነግም አቶ አሰፋ ጫቦ በሚፅፋቸው መራራ ሃቆች ሲቆስል ኖሯል ። ዛሬ አሰፋ ጫቦን አጥተነዋል ነገር ግን ስለአሟሟቱ እንድንጠይቅ የሚያስገድዱ ብዙ ጥርጣሬዎች አሉ ። አሰፋ ጫቦ ተገደለ ወይስ ” ሞተ? ” ። ይሄ እንቆቅልሽ ይፈታ ዘንድ ሁላችንም መጠየቅ እና ትክክለኛውን መልስ ማግኘት አለብን ።

ትውስታ… (አብደላ ዕዝራ)

13394118_1346035022079626_8563230783627582053_n“ጥሬ ሁል መብቀያ፣ መብሰያ ጊዜ አጣ፤
‘ካፍ ካፍ የሚለቅም’፥ የሰው ዶሮ መጣ።”
ብዬ የዛሬ ሶስት ዓመት የለጠፍኩት ላይ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየን ሀያሲ እና ፀሐፊ ጋሽ አብደላ ዕዝራ አስፍሮት ከነነበረው አስተያየት ፌስቡክ አስታወሰኝ። አስተያየቱን ከስር አስፍሬዋለሁ። ትንሹን ነገራችንን በቁምነገር መዝግበው እንደትልቅ እየቆጠሩልን የሚያበረቱንና የሚገስጹን ይብዙልን!
* * *
“ቀለማቱን ብቆጣጥር፥ ቤቱን ባስዉብ ባሰማምር፥
ቅኔ ዘረፋ ብማስን፥ ወርቁን ከሰሙ ብጋግር”… ያልከዉ ትዝ አለኝ።
“የብርሃን ልክፍት” እንደ ርዕስና ሽፋን የሚመጥነዉ የለም። ደበበ ቀድሞህ “የብርሃን ፍቅር”፥ አለማየሁ ገላጋይ ለጥቆ “የብርሃን ፈለጐች” ቢሉም፥ እንደ ርዕስ የልክፍትን [የብርሃን ልክፍት] ምትሃት ++ ያዉ እንደመጥምቁ በምናብ ወንዝ ተነክሮ ይሆናል። ጀርባዉም ይነባባል። ጨለማዉን ገምሶ የሚያንሰራራ የብርሃን ልክፍትአይለቅም።
የገዛሁት ሁለተኛዉን ዕትም ነበር። Oland በድሎሃል… ዉስጡን ለቄስ አስመሰለዉ፤ ግጥሞቹን ማለቴ አይደለም። scan ወይም ቀሺም ፎቶ ኮፒ መሰለ፤ በስንኝና በለጣቂዉ መካከል የተረሳዉ/የረገበዉ ክፍተት ገፀ ዉበቱን አደበዘዘዉ። የተፃፈበት ሆሄ ቢነበብም ቀለሙ [ካንተ ልዋስና] ወየበ። ሊትማንን “ገንዘቤን መልስ” አልለዉ-ጥቂት ግጥሞችህ እንቁ ሆነዉ ማን በፍራንክ የለዉጣቸዋል?
የመሰጠህን አንድ መንቶ ምረጥ በለኝ [] ሶስት ገፅ የወረረዉን የግጥሙን ድባብ የሚያባንንም፥ የሚያስተክዝ ነዉ። ተስፈንጥሮ የወጣ መንቶ አለ።
““እንኳን አደረሰህ” ከተንኳኳ በሬ
ያን ጊዜ እነቃለሁ፥ እሱ ነዉ ሀገሬ”
የተወሰኑ ግጥሞች ደግሜ የማነባቸዉ አሉ፤ ጥቂት የተንዛዙ እንደ መስለምለም ይከጅላቸዋል። ከመሰጠኝ አንዱ አሁን የሚታወሰኝ አጭር ግጥምህ ናት- “ፍርሃት” የምትለዉ። ለምን? እንዴት? ሰለመፅሐፍህ በሌላ ወቅት ሂስ መስል የተሰማኝን እገልጥለሃለሁ።
አሁን “ወርቁን ከሰሙ” የጋገርክበትን ከላይ የለገስከንን ዕምቅ መንቶ ልነካካዉ። አሻሚ ነዉ። ብርሃኑ ገበየሁ እንደሚለዉ “አሻሚነት ከአንድ ፍቺ በላይ ትርጓሜ መያዝ፥ ከግጥሙ ዐዉደንባብ በመነሳት ቁርጥ ያለ ትርጓሜ ለመስጥት አለመቻል” ነዉና እንደ አንባቢዉ ይነባበራል። ሁል ገድፈህ ሁሉ ቢሆን ዜማዉን አይጣረስም፤ ቀለም ሳይቆጠር እንዲሁ ሲደመጥ ያስታዉቃል። አለበለዝያ የ-ሁል- አደናጋሪነት የስንኙን ጠብታዎች ሊያመከን ነዉ።የተደራሲዉንም ትኩረት ይሻማል።
ገና እንደ አነበብኩት አዞ ትዝ አለኝ – አዞ እንባነቱ አይደለም – ሰፊ አፉን ከፍቶ ከጥርሶቹ መካከል አእዋፍ ጥሬ ስጋዉን ሲያስለቅሙ፤ ለአዞ እፎይታ ለነሱ መሰንበት። ይህ አንድምታ ነዉ።
“ካፍ ካፍ የሚለቅም የሰዉ ዶሮ መጣ” ግን ጉዳቱ ያሳስባል። አንድ የጥሬ ትርጉም “ያልተነካ ፥ አዲስ” ከሆነ አድገዉ ለወገን ምርኩዝ የሚሆኑትን ካከሰማቸዉ፥ በዘራፊ ማን ይመካል? ካፍ [ካፌ ባይሆንም] ከቀኝ ቢነበብ ፍካ ፍካ ሰለሚሆን ጮርቃዉን ብቻ አይደለም የፈካዉንም ሊለቃቀመ እንጂ። ይህ በደሉን አባባሰዉ። ከቀኝ ወደ ግራ ባይነበብም ሰሙ ወደ ወርቅ ሲመራም ነዉና ይነበብ።
ከጀርባዉ ከተስተዋለ ግን ብርቅ አንድምታ አለዉ። ዶሮ ጥሬ ለቅማ እኮ ነዉ [የአዳም ረታ ገፀባህሪይ – መዝገቡ- በልቶ የተደነቀበትን] የዕንቁላል ፍርፍር የምናገኘዉ። ጥሬ ተለቅሞ የሚጥም ከመቋደሻ እስከ ፈረሰኛ ለፋሲካ ወደ ብርሃነ ትንሳኤዉ የምንሻገርበት። “የሰዉ ዶሮ” የላመዉን፥ ያልሰለጠነዉን እየለቃቀመ እንደ ዕንቁላል እንደ ጫጩት ሊቀፈቅፋቸዉ ከቻለማ እሰየዉ ነዉ።
የግጥምህ አሻሚነት እየቆየ መዘርዘር፥ መነስነስ ይጀምራል። ይልቅ አሁን የመስፍን አሸብር ምጥን ግጥም ታሰሰኝ፤ በሱ ተመሰጥና ይብቃን።
“ጫጩቶቿን ብላ
ጭራ ልታበላ
“ቋቅ! ቁቅ!” እያለች፥
ይዛቸዉ ራቀች
ሄደች ኰበለለች፤
ያረባኋት ዶሮ
እንደወጣች ቀረች።”
—— // ——
ሀያሲ እና ፀሐፊ አብደላ ዕዝራ ግንቦት 28 ቀን 2008 ዓ/ም ነበር ከዚህ ዓለም በሞት የተለየን። ለኢትዮጵያ ስነጽሁፍ እድገት ትልቅ ሀብት ነበር።

ነፍሱ በሰላም ትረፍ!

Celebrate wo/men…

womens-day-2110796_960_720It is becoming customary that tragic stories of violence against women are blending our daily news and reports. The increased prevalence rate is somehow positive that it tells about the improved trend of reportings; hence, the incidence is increasingly alarming while it has to decrease with time and access to information.
 
Imagine the ‘unreported’ stories that happen regularly, and are settled by the intervention of go-betweens; think of women that are threatened by their loved ones, and ill-treated by a species of their kind; think of the society that points its fingers on ‘the victim’ than the ‘violent’; think of a girl’s voice that bounced back from the gates of our ears; recall the sympathies and society level embarrassing excuses for a violent: like ‘she shouldn’t wear a miniskirt’, ‘ምንም ሳታደርገውማ አይሆንም’.
 
The battle towards women’s rights is every human’s that we all should defend the human race, and speak up for the voiceless majority. Defending women is defending our own beings, houses, and communities. It is a risk that may jeopardize every household, the roots and branches of every family tree, and thus the minds of all.
 
How dare a bad father can talk about a bad leader? How dare a bad teacher can discipline his/her students? How dare a ‘corrupt’ husband/fiance to his love, can criticize a corrupt boss/authority? How dare a violent man can complain about other violence?
 
We all should empower women that it means empowering ourselves; it is empowering the society; it utilizing all our resources and excelling life; it is living life to the fullest; it is rationality; it is humanity; it is how it should gonna be. Life is unthinkable without wo/men!  
 
Taking the lion share, no wonder, women should uplift themselves; they should uplift men; they should uplift the society; they should cooperate in the process of generation replacement, and nurture uplifted children as an already determined fate, with the God’s will; that they should say “NO” for any oppression by their most intimate men, by people that they plan and commit their life with; …nor they should oppress anyone, and be civilly and intellectually arrogant.
 
They shouldn’t expect a miracle to come to their ways to triumph over life, nor wait for someone else to work for them; no one should expect of course! …we all should struggle rather; we all should get together, make comfortable ways and go through altogether. Then, the legacy for children will be a decent place, where life will be cherished, and death will be celebrated.
 
Wake up brother! “brother Jacob 😉 “, and uplift your home!, empower the executive of your home; never undermine her power, nor take her for granted; respect yourself and never objectify your woman, as saying ‘I love you’ for someone that yourself has dared to objectify is foolishness at its worst level. Never do that my man; never ever, even, when you think, on her foolishness.
 
Wake up sister! “sister 😉 “, and uplift your home and the lives inside it!, fortify your abilities, unleash the potentials in you, utilize resources, dig for opportunities to come to your ways, be respectful, be responsible and trusted, …and meet your soul truly! …that you will give birth for &rear an uplifted, other things being equal!
 
To respect each one another, and to contribute for the co
Let’s get changed to change.
Let’s get together, impact the society, and live together.
Let peace be upon our homes.
Let’s promise to ourselves to live in a peaceful state of minds.
We all deserve to live in a violent-free world; we can’t control what is in the world, but our homes/circles are our worlds.
 
Happy Women’s Day!
 
Happy Today! Happy Everyday!

Adwa

16999253_1552253318125754_8345020155766985375_nAdwa was not a war. It was an all-time phenomenal battle, where Ethiopians stood up for their dignity and curbed the colony of Italy. It was a victory of mankind in general, Africans in particular, and Ethiopians in very particular. Menelik II was the heroic leader that mobilized the resources, and made the victory true.
 
Adwa was a moment of truth that we have the power if we have the will… and hate has no place if people are united against invasion, of any form and level; and cruelty.
 
Ethiopia thought the world, in action 121 years ago that ‘no mountain is too high for people to climb, and no river is too deep to swim’. It showed once and for all that ‘the sky is the limit’ whatsoever; stated a bold, seemingly ‘most unlikely’ fact: if one is determined, all ceilings are glass.
 
It is akin to David and Goliath. In their battlefield near the valley of Elah, the game changer has been David’s faith in God and confidence, and its impact on his perspective towards the giant Goliath. He slung a stone at the giant Goliath’s head.
 
Likewise, the patriots of Adwa looked into the battle from mankind point of view, dignity point of view, love point of view, freedom point of view… and they chose to befriend with mankind than live in sycophancy in their own land.
 
They didn’t cross borders to fight, they counter-attacked the troop that traveled miles to them. They didn’t submissively bow for the flashy life, but they stood firm to defend humanity – in truth and in action. It was brave that they used shields to protect rifles, and spears to fight back.
 
They loved us to death by their integrity. They fought effectively for our dignity… and the answer has been Victory!

የሁለት ፕሮፌሰሮች ወግ…

 “ከቤተሰቤ መካከል አማርኛ የምችል እኔ ብቻ ነኝ።mqdefault
ሌሎች 13 ወንድምና እህቶቼ አማርኛን እንዳይሰሙም
እንዳይናገሩም አድርገን በጥሩ ሁኔታ አሳድገናቸዋል።
አሁን ያለዉ የቁቤ ትዉልድም ከሞላ ጎደል አማርኛን
የማይናገር የማይሰማ ጀግና ትዉልድ ሆኗል።”

~ ፕ/ር ህዝቅኤል ጋቢሳ (በOMN)

merera-gudina100

“ቋንቋን በአግባቡ ያለመጠቀም የኦሮሞ ሕዝብ ተገቢ የመብት ጥያቄዎችን ለሌሎች እንዳያስረዳ እንቅፋት ከሆኑበት ነገሮች አንዱ ይመስለኛል፡፡ በ1983ቱ የሽግግር ጉባዔ ላይ እነ ኦቦ ሌንጮ ለታ ለየት ለማት በአስተርጓሚ ለመናገር ሲሞክሩ፣ አቶ መለስ በመንዝአማርኛ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ሲፈልጥና ቆርጦ ሲቀጥል ነበር፡፡ ፓለቲካ ለሚያውቅና ለገባው ሰው፣ ኦሮሚፋ አንድ ቀን እንኳ በአደባባይ ይሰማልን የሚባል የአናሳ ቡድን ቋንቋ ሳይሆን ትልቁ የኢትዮጵያ ብሄር የሚናገረው ቋንቋ ነው፡፡ ሙዚየም ውስጥ ይቀርብኛል ተብሎ የሚሰጋለት ቋንቋ አይደለም፡፡ የቋንቋ ፖለቲካ የማይናቅ ባይሆንም፣ በተገቢው ጊዜና ቦታ ካልተጠቀሙ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ሊያመዝን ይችላል፡፡”

~ ፕ/ር መረራ ጉዲና – “የኢትዮጵያ ፓለቲካ ምስቅልቅል ጉዞና የሕይወቴ ትዝታዎች ከኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ እስከ ኢህአዲግ” ገፅ 225

ቋንቋ

መግባቢያ ነው። ክህሎት እንጂ እውቀት አይደለምና ባይችሉ አያሳፍርም። መቻሉም ቢያስደንቅና ቢጠቅም እንጂ፥ የተለየ ሆኖ የሚያስኮፍስ ነገር አይደለም። ሰው እንደዋለበትና እንደፈለገው ልክ የትኛውንም ቋንቋ ማወቅና በአግባቡ የመጠቀም ክህሎቱን ማሻሻል ይችላል። ብዙ ቋንቋ ባወቀ ቁጥር ግን የተሻለ መግባባት እና መፍትሄ ማምጣት ይችላል።

በተለይ፥ ቋንቋውን ሆነ ብሎ ላለመማር መጣርም ጉልበትና ጥረት ይጠይቃልና ራሱን የቻለ ድካም አለው። ማለዳ ማለዳ ተነስቶ፥ ልጆችን ስለጥላቻ መስበክ፣ እሱን ቋንቋ እንዳትናገሩ ብሎ መጨቆን፣ ጓደኞቻቸውን መምረጥ፣ ውሏቸው ላይ ጣልቃ መግባት… ሁሉ የመብት ጥሰቶች ሆነው ያስወቅሳሉ እንጂ፥ እንደጥሩ ገሪነት የሚያስደንቁ አይደሉም። ወላጅ/አሳዳጊ ከዚህ በላይ ሊበድልም አይችልም!

እኔ ኦሮሚኛ ለመማር ከምደክመው በላይ (አዲስ ቃል ብሰማ እና አፌ ውስጥ ቢገባ ለመጠቀም እደጋግመዋለሁ እንጂ ስለመርሳት አልጨነቅም) እነ ፕሮፌር እዝቅሔል ቤተሰብ ልጆቻቸው አማርኛ እንዳያውቁ የደከሙት ሲታሰብ ያስቆጫል። ልጆች ከሰው ጋር ተግባብተው እንዳይኖሩ መፍረድ ኅሊና ላለው ሰው ግፍ ነው።

በክልልስ እሺ፥ መንግስትም ለይስሙላ ፌደራሊዝሙ ሲል “በአፍ መፍቻ ቋንቋ አስተምራለሁ” ይላልና በዚያ ያልፋሉ። 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሲመጡ መግባባት ከባድ ይሆናል። ዩኒቨርስቲ ሲገቡም እንዲሁ ሆኖ ሰው ባያገል እንኳን ራስን ማሸሽም ይከሰታል። ሕብረተሰብ ካልተግባባ ደግሞ ግፈኞች ጥሩ ምሽግ ያገኛሉ።

ስለታሪክስ ቢሆን በአንድ ቋንቋ እና ወገን ብቻ የተነገረውን፣ እንደዶግማ ከመጋት፣ ብዙ ማስረጃዎች (resources) ያሉበትን ቋንቋ፥ “ላስተምር” ብሎ መጣር ቢቀር፣ “እንዳይማሩ” ብሎ መነሳት ክፋት እንጂ ሌላ ምን ምክንያት አለው?

በአሜሪካ

20160709_200649ፕሮፌሰሩ እዝቅሔል ገቢሳ፣ ካለክልሉ አስጠግታው፣ ቤት ንብረት አፍርቶ፣ “ሰዎችን ከክልላችን ውጡ” እያለ እንደልቡ እየተከፈተ በሚኖርባት እና በሚያስተምርባት አገረ አሜሪካ…

ሰሞኑን የሜሪላንድ የጤና መድኅን ዋስትና ማዕከል፣ ለደንበኞቹ የላከው ደብዳቤ ላይ ወደ 17 የሚጠጉ ቋንቋዎች (Bassa የሚባል ስሙን ሰምቼው የማላውቀው እና፣ ‘Khmer’ እና ‘Laotian’ የሚባሉ ቋንቋዎች፥ ፊደሎቻቸው እርስበርስ ተያይዘው ሸረሪት ቀለም ነክታ ወረቀቱ ላይ የሄደችበት መስለው የሚያስቁ ሳይቀሩ ተካተው) ተጠቅሞ ያስተላለፈውን መረጃ ተመልክቼ ነበር። ከቋንቋዎቹ ውስጥ፥ አማርኛ እና ኦሮሚኛም ተካተውበታል።

በአማርኛ የተጻፈው….

“ያለምንም ክፍያ በራስዎ ቋንቋ እገዛ የማግኘት መብት አለዎት። ስለማመልከቻዎ ወይም ከጤና ዋስትና ድርጅቱ ስለሚያገኙት ሽፋን ማንኛውም ጥያቄዎች ካሉዎት፣ ወይም ይህ ማሳወቂያ በግልፅ በተጠቀሰ ቀን ማድረግ ያለብዎ ነገር እንዳለ የሚያስገድድዎ ከሆነ፣ በተጠቀሰው የስልክ ቁጥር ለስትቴትዎ ወይም ለክልልዎ ደውለው ከአስተርጓሚ ጋር ይነጋገሩ።” ይላል።

20160813_193553አሜሪካ ውስጥ፣ ከቆሻሻ መጣያ ቅርጫቶች አንስቶ በተለያዩ ቦታዎች፥ የአማርኛንም ሆነ ሌሎች ቋንቋዎችን ተጠቅመው ለመግባባት ሲጥሩ ይታያል። በሂደቱ፥ የሚያስቁ አጠቃቀሞችም አይጠፉም።

ከገጠሙኝ መሀል፣ በ’ዋሽንግተን ኤቲካል ሶሳይቲ’ አዳራሽ መጸዳጃ ቤት ግድግዳ ላይ “Do not put paper towels in the toilets.” የሚለውን መልእክት በ5 የተለያዩ ቋንቋዎች ለማስተላለፍ ሙከራ ተደርጓል። በአማርኛ የተጻፈውን ስመለከተው፥ “ዶ ኖት ፑት ፓፐር ቶወልስ እን ቶእለፅ!” ይላል። 🙂

ስንት አለ ቶእለፅ ራስ አቦ!? …ሳይሾም የነገሰ፣ “እሟገትልሃለሁ” የሚለውን ኅብረተሰብ ሳያውቅ የሚንቧቸር የእንግዴ ልጅ!

Good news…

Habitamu-Ayalew.jpgThe long waiting and imploring have come to an end, finally! The cruels banned what shouldn’t be banned in the first place, – ‘traveling for better medication’, even traveling for leisure would have been up to the individual… now, they have ‘allowed’ and we’re happy that Habtamu Ayalew is safe in USA. This is an ever ugly drama: ‘they take our rights’, and when they give us back, ‘we celebrate’.

But if one can afford, why not even to the Mars, even to the Moon? What the hell should the government get to do with it? But this is how it is when ‘gun’ governs… it even would have been worse.

Hallelujah! And congrats for all who have been concerned. And all the best Habtish and family!

—-

Habtamu Ayalew, has beenformer spokesman of the opposition, Andenet (Unity), Party, and he was arrested on July 8, 2014 and charged with ‘terrorism for allegedly collaborating with the opposition Ginbot 7’, which the Ethiopian government has proclaimed as ‘a terrorist group’. Habtamu was detained at the notorious Maekelawi and Qilinto Prisons, where he was subjected to torture and other ill-treatment through denial of access to toilet facilities, ‘a situation that led to him to develop excruciatingly painful hemorrhoids’. He was banned from leaving the country because the prosecutor has appealed the ‘release from prison’ decision of the High Court. As known, his hemorrhoids were easily treatable, hadn’t it been left untreated to get worse to stage 3. 

 

 

የማንሳት ኃይል

እደጃፌ ወድቆ
ሳየው ኑሬ ኑሬ
ወዳጄ ሲያነሳው፣ ውድነቱን አውቆ
በንፍገት ደንብሬ፥
ልቤ ሊያብድ ተጨንቆ፣
ነፍሴ ሊበር ወልቆ፣ ስጋዬን አሳቅቆ።
እደጃፌ ወድቆ
“ለእግዜር” እንኳ ባልል፣
ለዐይኔ ተቆርቁሬ
ሳላነሳ ትቼው፣
ሲንደፋደፍ ከእግሬ
የቀረን ምስኪን ሰው
ስለነፍስ ያደረ ሳምራዊ ሲያነሳው፥
መጽደቁን ቆጥሬ፣
የደጉን ተጋድሎ፣ ባገር መወደሱን
በሀሳቤ ዘርዝሬ፣
በቁጭት ተቀጣሁ፣
ዋልኩኝ ተንጨርጭሬ
በክፋት ደንብሬ፣ በቅናት ታጥሬ።
* * *
ነገር ግን ይገርማል!
 
ወዳጅ ባየው ቅጽበት
ባነሳበት አፍታ፥
በተመኘው ጠዋት፣
ባጌጠበጥ ማታ፥
የጣሉት ይከብራል
ዋጋው ይጨምራል።
* * *
ጥፍጥናዬን ምጎ፣ መረቄን ጨርሶ
ከአውላላ ሜዳ ላይ የተፋኝ አንኳሶ፥
ስደክም የዘረረኝ፣ ስወድቅ የረገጠኝ
ስንከራተት ደጁ፣ ያልጣለልኝ ከእጁ
ያልነበርኩ ወዳጁ፥ ቆለለኝ ስነሳ
ካበኝ በየፈርጁ፣ ሰፈረልኝ ካሳ።
* * *
ለካስ ለመላ ነው የሚለው አገሩ፥
“የወደቀን አንሱ፣ የሞተን ቅበሩ”
ካለፈ እንዲማሩ፣ በወግ እንዲኖሩ
እጃት እንዲጥሩ፣ ዐይናት እንዲበሩ።
 
/ዮሐንስ ሞላ/