
ፈተናዎች…

ባለፈው ወር አካባቢ የቦርከና ድረ ገፅ ባለቤት የእለት ስራውን እያከናወነ እያለ ከሌላኛው የአለም ጫፍ ከወደ አውስትራሊያ አንድ አጠር ያለች መልእክት ትደርሰዋለች ። ይች መልእክት ቦርከና የመልእክት ሳጥን ውስጥ በገባችበት ሰአት በሌላኛው የአለም ጫፍ አንድ በሙሉ ጤንነት ላይ የሚገኝ ሰው ዳላስ ውስጥ ምናልባት ራሱ ያፈላውን ቡና ከሲጃራው ጋር እያወራረደ ይሆናል ወይም ደሞ ብዙውን ጊዜውን የሚያዘወትርበት ቤተ መፅሃፍት ቤት ውስጥ ይሆናል ። ሁለቱንም ልማዶቹን በጣም ይወዳቸዋል ። ይህ ሰው በሙሉ ጤንነት ይገኝ የነበረው አሰፋ ጫቦ ነበር ።
መልእክቷ ምን ትላለች?
የቦርከናው ድረ ገፅ ባለቤት መልእክቷን ሲከፍታት እንደዚህ ትላለች
” ሰላም ጠና ይስጥልኝ ። ስሜ ግሪጎሪ ማኬንዚ ይባላል ። አቶ አሰፋ ጫቦ ጋር እንተዋወቃለን ። ሁለታችንም በዓለም በቃኝ እስር ቤት ጓደኛ ነበርን ። እባክህ የአቶ አሰፋ ጫቦን የኢሜይል አድራሻ ላክልኝ። ከምኖርበት አውስትራሊያ ወደ አሜሪካ ስለምጓዝ አሰፋን ማግኘት እፈልጋለሁኝ ። ሁለታችንም ስላረጀን የመጨረሻ እድሌ ሊሆን ይችላል ። ” ይላል
ይች አጭር መልእክት የደረሰችው የቦርከናው ድሜጥሮስ ብርቁ ወድያውኑ ለአቶ አሰፋ በፌስ ቡክ ሜሴጂ በኩል የሚከተለውን መልእክት ይልካል :
” ጋሼ አሰፋ ሰላም ነዎት ወይ? አንድ ግሪጎሪ ማኬንዚ የሚባል ሰው ከወደ አውስትሪሊያ ኢሜሎትን ጠየቀኝ ። ሰውየው በአለም በቃኝ እስር ቤት አብረን አሳልፈናል እያለ ነው ። ጓደኛየ ነበሩ ብሏል ። ግለሰቡን ያውቁታል ወይ ? ” በማለት ይፅፍላቸዋል ።
አሰፋ ጫቦም ስሙን በማስታወስ ” አዎን ! በማእከላዊ እስር ቤት ካገኘኋቸው አዋቂ የምላቸው ሰዎች አንዱ ነው ፤ ኢሜይሌን ስጠው ” ብለው መለሱ።
የአቶ አሰፋን መልስ ያገኘው የቦርከናው ድረ ገፅ ባለቤት አቶ አሰፋ የሰጡትን የኢሜይል አድራሻ ለግሪጎሪ ማኬንዚ ይልክለታል ።
ከቀናት በኋላም አቶ አሰፋ ወደ ቦርከና በላኩት መልእክት ” ግሪጎሪ ማኬንዚ በስልክ እንዳገኛቸው እና ወደ አሜሪካ ሲመጣ ዳላስ ቴክሳስ ለመገናኘት እንደተቀጣጠሩ ይነግሩትና ። ” ምስጋና ጨምረው ይፅፉለታል ።
ቀድሞ በተያዘው ቀጠሮ መሰረት አቶ አሰፋ ጫቦ እና “ሊጎበኛቸው” ዳላስ ድረስ የሄደው ግሪጎር ማኬንዚ ማርች 27 ቀን ዳላስ (ዳውን ታውን) ተገናኙ። በወቅቱ ሁለቱ ግለሰቦች ሲገናኙ አቶ አሰፋ ጫቦ ምንም አይነት የህመምም ሆነ የድካም ምልክት ያልነበራቸው እና እንዲያውም ለእድሜያቸው በጣም ጠንካራ የሚባል ሁኔታ ላይ እንደነበሩ ነበሩ ።
ይሄንም የሚያረጋግጥ ምናልባት ከራት ሰዓት በፊት በሚመስል ሁኔታ አብረው የተነሱትንም ፎቶ ግራፍ አለ።
ሶስት ሰዓት በዘለቀው ቆይታቸው ፤ በእራት ሰዓት በአንድ የጣሊያን ሬስቶራንት ራት በልተው ፤ እንደገና ለመገናኘት ቀጠሮ ይዘው ተለያዮ።
በማግስቱ አቶ አሰፋ ጨቦ ታመው ሆስፒታል ሄዱ። አቶ አሰፋ ጫቦ የመጨረሻዋን ኤሜይል ለግሪጎሪ ፃፉ “በምግብ መመረዝ” ። እንደታመሙ እና ስለህመማቸው ስሜት በዝርዝር ከፃፉለት በኋላ ዳግም ሊያገኙት ያልቻሉበትን ምክንያት ሆስፒታል መግባታቸው እንደሆነ ገለፁለት ። ”
ከአውስትሪሊያ ወደ አሜሪካ አቶ አሰፋን ጫቦን ለማግኘት ብዙ ሺህዎች ማይል አቋርጦ ዳላስ የደረሰውና አብሮአቸው ራት የበላው ግሪጎር ማኬንዚ ምንም የሆነው ነገር የለም።
ከዚያ በኋላ አቶ አሰፋ ከሆስፒታል አልተመለሱም። የግሪጎሪ ማኬንዚን እራት ተከትሎ ወደ ሆስፒታል የገቡት አቶ አሰፋ ከሆስፒታሉ ድነው ሳይሆን የወጡት ህይወታቸው አልፎ ነበር ።
እንቆቅልሹ የሚጀምረው እዚህ ላይ ነው ።
ለአለፉት 40 አመታት አቶ አሰፋ ጫቦ ከተለያዩ የፖለቲካ ሃይሎች ጋር ግልፅና ስውር ሽኩቻ ሲያደርግ ቆይቷል ። ዋጋም ከፍሎበታል ። ኢትዮጵያ ውስጥ እና በአካባቢው ያሉ የፖለቲካ ሃይሎች ወያኔ ፣ ኦነግ ፣ሸአቢያ ፣ ኢህአፓ እና መኢሶኖች አሰፋ ጫቦ ላይ ብዙ ክሶችን ፅፈውበታል ። እሱም የሚያውቀውን የድርጅቶችን ገበና ሳያቅማማ ሲፅፍ ነበር ። እነዚህ ፓርቲዎች በግለሰብ ደረጃ እንደ አሰፋ ጫቦ በእጅጉ የሚፈሩት አልነበረም፡፡ የሸአቢያን ፣ የወያኔንና የኦነግን ሴራ የሚያጋልጠው ፅሁፉ ፅፎ ካሰራጨና በመላው አለም መነጋገሪያ ከሆነ እንኳን ሁለት ወር አይሞላውም ነበር ።
አሰፋ ጫቦ በብሩህ አዕምሮውና በላቀ የእውቀት ደረጃው ብዙዎቹን ፖለቲከኞች በእጥፍ ድርቡ ያስከነዳቸው ነበር ፡፡ በዚህ የተነሳም አሰፋ ጫቦን ለአመታት ሲሰሩት የነበረውን ድብቅ ሴራ አውጥቶብናል ገና ወደፊትም ያወጣብናል እያሉ አጥብቀው ይፈሩትና አምርረው ይጠሉት ነበር ።
አሰፋ ጫቦ ጠንቃቃና የማስታወስ ችሎታ የነበረው አዛውንት ስለነበር በኢትዮጵያ ውስጥ እና በኢትዮጵያ ላይ የተሰሩ የድብቅ ሴራዎችን በጥንቃቄ ይዟቸው ኖሮ እያወጣ መጎልጎል ጀመረ ። በመለስ ዜናዊ የውሸት ክስ ሀገር የተባረረው አሰፋ ጫቦ በአሜሪካ አገር በስደት መኖር ጀመረ፡፡ የተለያዩ የፖለቲካ ሃይሎች ግን በብዙ ሺ ኪሎ ሜትሮች ርቆ በሰው ሀገር የሚኖር ቢሆንም የአሰፋ ጫቦ ነገር እንቅልፍ ሊሰጣቸው እንዳልቻለ ብዙ ጠቋሚ ምክንያቶች ነበሩ ።፡ አቶ አሰፋ ጫቦ በተለያዬ ጊዜ በሚፅፋቸውና በሚያጋልጣቸው ድብቅ ሴራዎች “የቀን ቅዠት ሆኖ እያባነነና እያስበረገጋቸው እንደነበር ይታወቃል። ሌሎቹንም የተደበቁ ሴራዎች እየፃፈ እንደነበር ተናግሯል ።
የአቶ አሰፋ ጫቦ የማስታወሻ ደብተር ብዙ ጉዳዮችን አጭቂ የያዘ እንደነበር መገመት አይከብድም ። የኢትዮጵያ ፖለቲካ
እንደ ቆሰለ ጅብ የመበላላት አባዜ የተጠናወተው ነው ። ሸፍጡን እና ሴራውን ለመደበቅ አንዱን ገድሎ ስልጣኑን ማደላደል የተለመደ ነው ። ይሄ ለአመታት የተለመደ መርዘኛ ሂደቱን ቀጥሏል ። ከአንድ ሰሞን ከንፈር መምጠጥ ባለፈ “ ይሄ ሰው እንደት ሞተ? “ለምን ተገደለ?” በማን ተገደለ? ገዳዩ ለፍርድ ይቅረብ ወዘተ” የሚል ባህል የለንም ።
የአሰፋ ጫቦ ጉዳይ ገዳይ ተገዳይ ድራማ ያለበት መስሎ ይሰማኛል ፡፡ በዚህ የገዳይ ተገዳይ ድራማ ውስጥ ብዙ ተሳታፊዎችን መጥቀስ ይቻላል ። አሰፋ ጫቦ በብእሩ ጫፍ ያቆሰላቸው ብዙ ናቸው ። “የትዝታ ፈለግ ” በሚለው መፅሃፉ CIA ኢትዮጵያን ለማፍረስ ሱዳን ካርቱም ላይ መሰርቶት የነበረውን ጣቢያ አጋልጧል ።
“የተሰነይ ጉባኤ ” በሚለው ፅሁፉ ወያኔ ፣ሸአቢያ እና ኦነግ በኢትዮጵያ ላይ የሰሩትን ሴራ ለህዝቡ አሳውቋል ። ለወደፊቱም የሚያጋልጣቸው ብዙ ሚስጥሮች እንዳሉት እና እያዘጋጃቸው እንደነበር ነግሮናል ።
ስታሊን ከአባት ሀገር ያባረረውን ሊዮን ትሮትስኪ በብዙ ሺ ኪሎ ሜትሮች ርቆ በሰው ሀገር ሜክሲኮ የሚኖር ቢሆንም የሊዮን ትሮትስኪ ነገር እንቅልፍ ሊሰጠው ስላልቻለ በመጥረቢያ አስፈልጦ አስገደለው ። ወያኔ በኬኒያ እና በሱዳን የሚኖሩ ተራ ስደተኞች እረፍት ሲነሷት ወደ አገሮቹ ጎራ በማለት እንደምትገድል ይታወቃል ። CIA ም ቢሆን ጠላቴ ትንሽ ነው ብሎ አይንቅም ። ኦነግም አቶ አሰፋ ጫቦ በሚፅፋቸው መራራ ሃቆች ሲቆስል ኖሯል ። ዛሬ አሰፋ ጫቦን አጥተነዋል ነገር ግን ስለአሟሟቱ እንድንጠይቅ የሚያስገድዱ ብዙ ጥርጣሬዎች አሉ ። አሰፋ ጫቦ ተገደለ ወይስ ” ሞተ? ” ። ይሄ እንቆቅልሽ ይፈታ ዘንድ ሁላችንም መጠየቅ እና ትክክለኛውን መልስ ማግኘት አለብን ።
“ከቤተሰቤ መካከል አማርኛ የምችል እኔ ብቻ ነኝ።
ሌሎች 13 ወንድምና እህቶቼ አማርኛን እንዳይሰሙም
እንዳይናገሩም አድርገን በጥሩ ሁኔታ አሳድገናቸዋል።
አሁን ያለዉ የቁቤ ትዉልድም ከሞላ ጎደል አማርኛን
የማይናገር የማይሰማ ጀግና ትዉልድ ሆኗል።”
~ ፕ/ር ህዝቅኤል ጋቢሳ (በOMN)
“ቋንቋን በአግባቡ ያለመጠቀም የኦሮሞ ሕዝብ ተገቢ የመብት ጥያቄዎችን ለሌሎች እንዳያስረዳ እንቅፋት ከሆኑበት ነገሮች አንዱ ይመስለኛል፡፡ በ1983ቱ የሽግግር ጉባዔ ላይ እነ ኦቦ ሌንጮ ለታ ለየት ለማት በአስተርጓሚ ለመናገር ሲሞክሩ፣ አቶ መለስ በመንዝአማርኛ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ሲፈልጥና ቆርጦ ሲቀጥል ነበር፡፡ ፓለቲካ ለሚያውቅና ለገባው ሰው፣ ኦሮሚፋ አንድ ቀን እንኳ በአደባባይ ይሰማልን የሚባል የአናሳ ቡድን ቋንቋ ሳይሆን ትልቁ የኢትዮጵያ ብሄር የሚናገረው ቋንቋ ነው፡፡ ሙዚየም ውስጥ ይቀርብኛል ተብሎ የሚሰጋለት ቋንቋ አይደለም፡፡ የቋንቋ ፖለቲካ የማይናቅ ባይሆንም፣ በተገቢው ጊዜና ቦታ ካልተጠቀሙ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ሊያመዝን ይችላል፡፡”
~ ፕ/ር መረራ ጉዲና – “የኢትዮጵያ ፓለቲካ ምስቅልቅል ጉዞና የሕይወቴ ትዝታዎች ከኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ እስከ ኢህአዲግ” ገፅ 225
ቋንቋ
መግባቢያ ነው። ክህሎት እንጂ እውቀት አይደለምና ባይችሉ አያሳፍርም። መቻሉም ቢያስደንቅና ቢጠቅም እንጂ፥ የተለየ ሆኖ የሚያስኮፍስ ነገር አይደለም። ሰው እንደዋለበትና እንደፈለገው ልክ የትኛውንም ቋንቋ ማወቅና በአግባቡ የመጠቀም ክህሎቱን ማሻሻል ይችላል። ብዙ ቋንቋ ባወቀ ቁጥር ግን የተሻለ መግባባት እና መፍትሄ ማምጣት ይችላል።
በተለይ፥ ቋንቋውን ሆነ ብሎ ላለመማር መጣርም ጉልበትና ጥረት ይጠይቃልና ራሱን የቻለ ድካም አለው። ማለዳ ማለዳ ተነስቶ፥ ልጆችን ስለጥላቻ መስበክ፣ እሱን ቋንቋ እንዳትናገሩ ብሎ መጨቆን፣ ጓደኞቻቸውን መምረጥ፣ ውሏቸው ላይ ጣልቃ መግባት… ሁሉ የመብት ጥሰቶች ሆነው ያስወቅሳሉ እንጂ፥ እንደጥሩ ገሪነት የሚያስደንቁ አይደሉም። ወላጅ/አሳዳጊ ከዚህ በላይ ሊበድልም አይችልም!
እኔ ኦሮሚኛ ለመማር ከምደክመው በላይ (አዲስ ቃል ብሰማ እና አፌ ውስጥ ቢገባ ለመጠቀም እደጋግመዋለሁ እንጂ ስለመርሳት አልጨነቅም) እነ ፕሮፌር እዝቅሔል ቤተሰብ ልጆቻቸው አማርኛ እንዳያውቁ የደከሙት ሲታሰብ ያስቆጫል። ልጆች ከሰው ጋር ተግባብተው እንዳይኖሩ መፍረድ ኅሊና ላለው ሰው ግፍ ነው።
በክልልስ እሺ፥ መንግስትም ለይስሙላ ፌደራሊዝሙ ሲል “በአፍ መፍቻ ቋንቋ አስተምራለሁ” ይላልና በዚያ ያልፋሉ። 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሲመጡ መግባባት ከባድ ይሆናል። ዩኒቨርስቲ ሲገቡም እንዲሁ ሆኖ ሰው ባያገል እንኳን ራስን ማሸሽም ይከሰታል። ሕብረተሰብ ካልተግባባ ደግሞ ግፈኞች ጥሩ ምሽግ ያገኛሉ።
ስለታሪክስ ቢሆን በአንድ ቋንቋ እና ወገን ብቻ የተነገረውን፣ እንደዶግማ ከመጋት፣ ብዙ ማስረጃዎች (resources) ያሉበትን ቋንቋ፥ “ላስተምር” ብሎ መጣር ቢቀር፣ “እንዳይማሩ” ብሎ መነሳት ክፋት እንጂ ሌላ ምን ምክንያት አለው?
በአሜሪካ…
ፕሮፌሰሩ እዝቅሔል ገቢሳ፣ ካለክልሉ አስጠግታው፣ ቤት ንብረት አፍርቶ፣ “ሰዎችን ከክልላችን ውጡ” እያለ እንደልቡ እየተከፈተ በሚኖርባት እና በሚያስተምርባት አገረ አሜሪካ…
ሰሞኑን የሜሪላንድ የጤና መድኅን ዋስትና ማዕከል፣ ለደንበኞቹ የላከው ደብዳቤ ላይ ወደ 17 የሚጠጉ ቋንቋዎች (Bassa የሚባል ስሙን ሰምቼው የማላውቀው እና፣ ‘Khmer’ እና ‘Laotian’ የሚባሉ ቋንቋዎች፥ ፊደሎቻቸው እርስበርስ ተያይዘው ሸረሪት ቀለም ነክታ ወረቀቱ ላይ የሄደችበት መስለው የሚያስቁ ሳይቀሩ ተካተው) ተጠቅሞ ያስተላለፈውን መረጃ ተመልክቼ ነበር። ከቋንቋዎቹ ውስጥ፥ አማርኛ እና ኦሮሚኛም ተካተውበታል።
በአማርኛ የተጻፈው….
“ያለምንም ክፍያ በራስዎ ቋንቋ እገዛ የማግኘት መብት አለዎት። ስለማመልከቻዎ ወይም ከጤና ዋስትና ድርጅቱ ስለሚያገኙት ሽፋን ማንኛውም ጥያቄዎች ካሉዎት፣ ወይም ይህ ማሳወቂያ በግልፅ በተጠቀሰ ቀን ማድረግ ያለብዎ ነገር እንዳለ የሚያስገድድዎ ከሆነ፣ በተጠቀሰው የስልክ ቁጥር ለስትቴትዎ ወይም ለክልልዎ ደውለው ከአስተርጓሚ ጋር ይነጋገሩ።” ይላል።
አሜሪካ ውስጥ፣ ከቆሻሻ መጣያ ቅርጫቶች አንስቶ በተለያዩ ቦታዎች፥ የአማርኛንም ሆነ ሌሎች ቋንቋዎችን ተጠቅመው ለመግባባት ሲጥሩ ይታያል። በሂደቱ፥ የሚያስቁ አጠቃቀሞችም አይጠፉም።
ከገጠሙኝ መሀል፣ በ’ዋሽንግተን ኤቲካል ሶሳይቲ’ አዳራሽ መጸዳጃ ቤት ግድግዳ ላይ “Do not put paper towels in the toilets.” የሚለውን መልእክት በ5 የተለያዩ ቋንቋዎች ለማስተላለፍ ሙከራ ተደርጓል። በአማርኛ የተጻፈውን ስመለከተው፥ “ዶ ኖት ፑት ፓፐር ቶወልስ እን ቶእለፅ!” ይላል። 🙂
ስንት አለ ቶእለፅ ራስ አቦ!? …ሳይሾም የነገሰ፣ “እሟገትልሃለሁ” የሚለውን ኅብረተሰብ ሳያውቅ የሚንቧቸር የእንግዴ ልጅ!
The long waiting and imploring have come to an end, finally! The cruels banned what shouldn’t be banned in the first place, – ‘traveling for better medication’, even traveling for leisure would have been up to the individual… now, they have ‘allowed’ and we’re happy that Habtamu Ayalew is safe in USA. This is an ever ugly drama: ‘they take our rights’, and when they give us back, ‘we celebrate’.
But if one can afford, why not even to the Mars, even to the Moon? What the hell should the government get to do with it? But this is how it is when ‘gun’ governs… it even would have been worse.
Hallelujah! And congrats for all who have been concerned. And all the best Habtish and family!
—-
Habtamu Ayalew, has beenformer spokesman of the opposition, Andenet (Unity), Party, and he was arrested on July 8, 2014 and charged with ‘terrorism for allegedly collaborating with the opposition Ginbot 7’, which the Ethiopian government has proclaimed as ‘a terrorist group’. Habtamu was detained at the notorious Maekelawi and Qilinto Prisons, where he was subjected to torture and other ill-treatment through denial of access to toilet facilities, ‘a situation that led to him to develop excruciatingly painful hemorrhoids’. He was banned from leaving the country because the prosecutor has appealed the ‘release from prison’ decision of the High Court. As known, his hemorrhoids were easily treatable, hadn’t it been left untreated to get worse to stage 3.