ከመጽሐፍቱ መቃጠል ባሻገር… ከ”ጳጳሱ ቅሌት” እስከ “ጳጳሱ ስኬት” ቢታሰብስ | Episode 4

“ጎዳናው እስኪቋጭ” የአሳዬ ደርቤ አዲስ መጽሐፍ

69249314_2438420469722569_6256019960007491584_nሽግግሩ ከተከሰተበት ጊዜ አንስቶ በየቀኑ የሚሰሙ ቅስም ሰባሪ ሰበር-ዜናዎች ከመብዛታቸው የተነሳ ለማስታወስ ያዳግታል፡፡ እመርታዎቹ ደግሞ የማይታዩና የማይጨበጡ በመሆናቸው ማይክሮስኮፕ ላይ ተጥዶ ምርምርና ጥናት ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
ከለውጡ ወዲህ የተቀጠፉት ነፍሶች ይሄን ለውጥ ለማምጣት ከተሰውት እየበለጠ ነው፡፡ ይሄም ሆኖ ግን ሰውዬው በምታለቅስ አገር ላይ ፈገግ እንዳለ ቀርቷል፡፡ ሁሉም ነገር የሚሆነው በእሱ ይሁንታ ይመስል፣ በተደናገረው ሕዝብ መሀከል በሁለት ዙር ግንብ ካሳጠረው ቤተ-መንግሥቱ ውስጥ ሆኖ በቃላት ይፈላሰፋል፡፡

*

የመጻፍ ሙዳችን እየመጣ ነው፡፡
ስለምን እንጻፍ? ስለምን እንፈላሰፍ?
“ሽግግር- ከችግር ወደ ችግር” የሚል ርዕስ አስምረን ችግሮቻችንን እንዘርዝር?
ነው ወይስ…
“ለውጥ- ከማጥ ወደ ማጥ” የሚል አጀንዳ ይዘን “እንደ አገር” አብረን እንስመጥ?

ድል- ከትግል ወደ ትግል
ድልድይ- ከገደል ወደ ገደል
ምናምን፣ ምናምን እንበል?

ወይስ?

ለውጡ እንዳይቀለበስ
ትችታችን ጋብ አርገን- ንፋሱን ጋልበን እንንፈስ?

*

እኛን ያላዩ ፈረንጆች-በእውቀት፣ በሀብቱ የታደሉ
“A problem well-stated is a problem half solved” ይላሉ፤
“ሙሉ በሙሉ የታወቀ ችግር በከፊል ምላሽ አግኝቷል” እንደ ማለት፤
ታዲያ የኛ ደዌ እና ተውሳክ- ሙሉ በሙሉ ታውቆ ሳል- እንዴት መፍትሄ ታጣለት?
ለዶክተሩ የነገርነው በሽታችን ሊድን ቀርቶ ስለምን ነው የባሰባት?
መልሱ ቀላል ነው!
በሽታችን ገሃድ ወጥቶ-እንደ ብቅል- ከጸሐይ ላይ ቢነጠፍም
መርፌና ሐኪም ከለገመ- እንኳን ታፋ- ቅቤ አይወጋም፡፡
በሺህ ቃላት ቢቀባቡት- የመርዝ ውህድ- ሽሮፕ ሆኖ አይፈውስም፡፡
በመሆኑም…
ዶክተር በምድሩ ሳለ- ቅስቻችንን ያበረታው- የተያዝነው በጣር፣ ሲቃ
“ሕመማችን ታውቆ ሳለ- መዳኒቱን ተነፍገን ነው” ብዬ ላብቃ፡፡

ትውስታ… (አብደላ ዕዝራ)

13394118_1346035022079626_8563230783627582053_n“ጥሬ ሁል መብቀያ፣ መብሰያ ጊዜ አጣ፤
‘ካፍ ካፍ የሚለቅም’፥ የሰው ዶሮ መጣ።”
ብዬ የዛሬ ሶስት ዓመት የለጠፍኩት ላይ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየን ሀያሲ እና ፀሐፊ ጋሽ አብደላ ዕዝራ አስፍሮት ከነነበረው አስተያየት ፌስቡክ አስታወሰኝ። አስተያየቱን ከስር አስፍሬዋለሁ። ትንሹን ነገራችንን በቁምነገር መዝግበው እንደትልቅ እየቆጠሩልን የሚያበረቱንና የሚገስጹን ይብዙልን!
* * *
“ቀለማቱን ብቆጣጥር፥ ቤቱን ባስዉብ ባሰማምር፥
ቅኔ ዘረፋ ብማስን፥ ወርቁን ከሰሙ ብጋግር”… ያልከዉ ትዝ አለኝ።
“የብርሃን ልክፍት” እንደ ርዕስና ሽፋን የሚመጥነዉ የለም። ደበበ ቀድሞህ “የብርሃን ፍቅር”፥ አለማየሁ ገላጋይ ለጥቆ “የብርሃን ፈለጐች” ቢሉም፥ እንደ ርዕስ የልክፍትን [የብርሃን ልክፍት] ምትሃት ++ ያዉ እንደመጥምቁ በምናብ ወንዝ ተነክሮ ይሆናል። ጀርባዉም ይነባባል። ጨለማዉን ገምሶ የሚያንሰራራ የብርሃን ልክፍትአይለቅም።
የገዛሁት ሁለተኛዉን ዕትም ነበር። Oland በድሎሃል… ዉስጡን ለቄስ አስመሰለዉ፤ ግጥሞቹን ማለቴ አይደለም። scan ወይም ቀሺም ፎቶ ኮፒ መሰለ፤ በስንኝና በለጣቂዉ መካከል የተረሳዉ/የረገበዉ ክፍተት ገፀ ዉበቱን አደበዘዘዉ። የተፃፈበት ሆሄ ቢነበብም ቀለሙ [ካንተ ልዋስና] ወየበ። ሊትማንን “ገንዘቤን መልስ” አልለዉ-ጥቂት ግጥሞችህ እንቁ ሆነዉ ማን በፍራንክ የለዉጣቸዋል?
የመሰጠህን አንድ መንቶ ምረጥ በለኝ [] ሶስት ገፅ የወረረዉን የግጥሙን ድባብ የሚያባንንም፥ የሚያስተክዝ ነዉ። ተስፈንጥሮ የወጣ መንቶ አለ።
““እንኳን አደረሰህ” ከተንኳኳ በሬ
ያን ጊዜ እነቃለሁ፥ እሱ ነዉ ሀገሬ”
የተወሰኑ ግጥሞች ደግሜ የማነባቸዉ አሉ፤ ጥቂት የተንዛዙ እንደ መስለምለም ይከጅላቸዋል። ከመሰጠኝ አንዱ አሁን የሚታወሰኝ አጭር ግጥምህ ናት- “ፍርሃት” የምትለዉ። ለምን? እንዴት? ሰለመፅሐፍህ በሌላ ወቅት ሂስ መስል የተሰማኝን እገልጥለሃለሁ።
አሁን “ወርቁን ከሰሙ” የጋገርክበትን ከላይ የለገስከንን ዕምቅ መንቶ ልነካካዉ። አሻሚ ነዉ። ብርሃኑ ገበየሁ እንደሚለዉ “አሻሚነት ከአንድ ፍቺ በላይ ትርጓሜ መያዝ፥ ከግጥሙ ዐዉደንባብ በመነሳት ቁርጥ ያለ ትርጓሜ ለመስጥት አለመቻል” ነዉና እንደ አንባቢዉ ይነባበራል። ሁል ገድፈህ ሁሉ ቢሆን ዜማዉን አይጣረስም፤ ቀለም ሳይቆጠር እንዲሁ ሲደመጥ ያስታዉቃል። አለበለዝያ የ-ሁል- አደናጋሪነት የስንኙን ጠብታዎች ሊያመከን ነዉ።የተደራሲዉንም ትኩረት ይሻማል።
ገና እንደ አነበብኩት አዞ ትዝ አለኝ – አዞ እንባነቱ አይደለም – ሰፊ አፉን ከፍቶ ከጥርሶቹ መካከል አእዋፍ ጥሬ ስጋዉን ሲያስለቅሙ፤ ለአዞ እፎይታ ለነሱ መሰንበት። ይህ አንድምታ ነዉ።
“ካፍ ካፍ የሚለቅም የሰዉ ዶሮ መጣ” ግን ጉዳቱ ያሳስባል። አንድ የጥሬ ትርጉም “ያልተነካ ፥ አዲስ” ከሆነ አድገዉ ለወገን ምርኩዝ የሚሆኑትን ካከሰማቸዉ፥ በዘራፊ ማን ይመካል? ካፍ [ካፌ ባይሆንም] ከቀኝ ቢነበብ ፍካ ፍካ ሰለሚሆን ጮርቃዉን ብቻ አይደለም የፈካዉንም ሊለቃቀመ እንጂ። ይህ በደሉን አባባሰዉ። ከቀኝ ወደ ግራ ባይነበብም ሰሙ ወደ ወርቅ ሲመራም ነዉና ይነበብ።
ከጀርባዉ ከተስተዋለ ግን ብርቅ አንድምታ አለዉ። ዶሮ ጥሬ ለቅማ እኮ ነዉ [የአዳም ረታ ገፀባህሪይ – መዝገቡ- በልቶ የተደነቀበትን] የዕንቁላል ፍርፍር የምናገኘዉ። ጥሬ ተለቅሞ የሚጥም ከመቋደሻ እስከ ፈረሰኛ ለፋሲካ ወደ ብርሃነ ትንሳኤዉ የምንሻገርበት። “የሰዉ ዶሮ” የላመዉን፥ ያልሰለጠነዉን እየለቃቀመ እንደ ዕንቁላል እንደ ጫጩት ሊቀፈቅፋቸዉ ከቻለማ እሰየዉ ነዉ።
የግጥምህ አሻሚነት እየቆየ መዘርዘር፥ መነስነስ ይጀምራል። ይልቅ አሁን የመስፍን አሸብር ምጥን ግጥም ታሰሰኝ፤ በሱ ተመሰጥና ይብቃን።
“ጫጩቶቿን ብላ
ጭራ ልታበላ
“ቋቅ! ቁቅ!” እያለች፥
ይዛቸዉ ራቀች
ሄደች ኰበለለች፤
ያረባኋት ዶሮ
እንደወጣች ቀረች።”
—— // ——
ሀያሲ እና ፀሐፊ አብደላ ዕዝራ ግንቦት 28 ቀን 2008 ዓ/ም ነበር ከዚህ ዓለም በሞት የተለየን። ለኢትዮጵያ ስነጽሁፍ እድገት ትልቅ ሀብት ነበር።

ነፍሱ በሰላም ትረፍ!

መጽሐፍት ሲያዞሩ…

n1704ፀሐፊውን… የቻሉትን አሰሩ፣ የቻሉትን አባረሩ፣ የቻሉትን ደግሞ ለማስፈራራት ላይ ታች አሉ። የቻሉትን የሚፈልጉትን እንዲጽፍ አድርገው እቅፍ ድግፍ አድርገው ያዙት።
 
የመጽሐፍትን መታተም ለማስታጎልና የፀሐፊዎችን ቅስም ለመስበር፥ የመጽሐፍት ህትመት ዋጋን በወረቀት እና በሰበብ አስባብኩ ከፍ አደረጉት።
 
ነባር መጽሐፍትን በጨረታ እስከመሸጥ ድረስ፥ የአገራዊና ወቅታዊ ጉዳዮች መጽሐፍትን ድራሽ ለማጥፋት የሚችሉትን ሁሉ አደረጉ። ከነሱ ሀሳብ የተለየው ላይ ሁሉ ጥርሳቸውን ነከሱበት።
 
“ለሽብር የሚያነሳሱ መጽሐፍት” ብለው በራሳቸው ጊዜ ተሸብረው፣ ሕብረተሰቡ እንዲሸበር እና ተሸማቆ እንዲኖር፣ ሲያነብም እንዲሳቀቅ አዋጅ አንጋጉ።
 
ይኸው ደግሞ፥ መጽሐፍ አዙረው እውቀትን በማስፋፋትና ራሳቸውን በመደጎም የሥራ መስክ ላይ የተሰማሩ ምስኪን መጽሐፍት አዟሪዎችን ማሰር ጀመሩ።
 
የሪፖርተር ጋዜጣ ዜና እንዲህ ይነበባል….

አመፅ ቀስቃሽ ናቸው የተባሉ መጻሕፍት በመሸጥ የተጠረጠሩ አዟሪዎች ታሰሩ

ኅብረተሰቡን ለአመፅ የሚገፋፉና ግጭት ሊፈጥሩ የሚችሉ መጻሕፍት በማዘዋወርና በመሸጥ የተጠረጠሩ መጽሐፍት አዟሪዎች፣ ከነሐሴ 14 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ መታሰራቸው ታወቀ፡፡

ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ መጻሕፍት አዟሪዎች በተለያዩ ፖሊስ ጣቢያዎች መታሰራቸውንና በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ ችሎት ቀርበው ጊዜ ቀጠሮ እንደተጠየቀባቸው ቤተሰቦቻቸው ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡

አዟሪዎቹ የተጠረጠሩት ሕዝብ የሚያነሳሱና አመፅ የሚቀሰቅሱ መጣጥፎችን በፍትሕ ጋዜጣ ላይ በማተም ክስ ተመሥርቶበት የሦስት ዓመታት ጽኑ እስራት የተፈረደበት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ በቅርቡ ‹‹የፈራ ይመለስ›› በሚል ርዕስ ያሳተመውን መጽሐፍ፣ ፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ ‹‹የኦሮሞና አማራ የዘር ግንድ›› በሚል ርዕስ ያሳተሙት መጽሐፍና ጋዜጠኛ ሙሉ ቀን ተስፋው ‹‹የዘመኑ ጥፋት›› በሚል ርዕስ ያሳተመውን መጽሐፍ በማዞር ሲሸጡ ስለተገኙ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ጋዜጠኛ ተመስገን ቀደም ብሎ ክስ ተመሥርቶበትና ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ ቅጣት የተጣለበትን መጣጥፍና በድጋሚ በመጽሐፍ መልክ ያሳተመውን መጽሐፍ ማሠራጨት ወንጀል መሆኑን ፖሊስ ለፍርድ ቤት ማስረዳቱ ታውቋል፡፡ ሌሎቹም የተጠቀሱት መጻሕፍት አመፅ ቀስቃሽ መሆናቸውን በመግለጽ መሠራጨታቸው ተገቢ አለመሆኑን ፖሊስ ለፍርድ ቤት አስረድቶ፣ መጻሕፍቱ ሲታተሙ ያተማቸው ማተሚያ ቤት በመጽሐፉ ላይ መግለጽ የነበረባቸው ቢሆንም ሳይገልጹ መቅረታቸውንም አክሏል፡፡ ይኼም ሆን ተብሎ መንግሥት ቁጥጥር እንዳያደርግ በድብቅ የሚሠራ ሕገወጥ ተግባር መሆኑን በማስረዳት፣ ለተጨማሪ ምርመራ ተጨማሪ ጊዜ መጠየቁ ተገልጿል፡፡

የተወሰኑ አዟሪዎች መጻሕፍቶች ተነጥቀው ሁለተኛ እንዳያዞሩ ፈርመው መለቀቃቸውንና ማተሚያ ቤቱን እንዲጠቁሙ ተገደው እንደነበር ተናግረዋል፡፡ ሐሙስ ነሐሴ 18 ቀን 2008 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀርበው ጊዜ ቀጠሮ የተጠየቀባቸው መጻሕፍት አዟሪዎች ሰኞ ነሐሴ 23 ቀን 2008 ዓ.ም. በድጋሚ ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ታውቋል፡፡

አሜሪካ ድምጽ ሬድዮም ቀድሞ እንዲህ ዘግቦት ነበር…

መጽሐፍ አዟሪዎቹ በተለይ የተመስገን ደሳለኝ፣ የሙሉጌታ ሉሌና የዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ መጽሐፍ መሸጥ እንዳልቻሉ እነዚህን መጽሐፍትና ሌሎች የታሪክና የፖለቲካ መጽሐፍት ይዘው ሲገኙ እንደሚደበደቡ፣ እንደሚታሠሩና አንዳንዴም ለመለቀቅ ከደንብ አስከባሪዎች ጉቦ እንደሚጠየቁ ተናገሩ።

‘መጽሐፍቱን ማዞር ወንጀል ቢሆን’ እንኳን፥ በጎልማሶች ት/ት (መሰረተ ትምህርት adult education) ፕሮግራም እንኳን ማንበብና መጻፍ ያላስተማሩትን ዜጋ ምን ብለው “አመጽ ቀስቃሽ” መጽሐፍ ይዘህ ዞረኻል ብለው ያስሩታል? ያዋክቡታል? ይቀጡታል?
“አህያውን ፈርቶ ዳውላውን” አሉ። ከቻሉ ሀሳብን ማሰሩን አይሞክሩትም ነበር?!