Tag: Books
የጠይም በረንዳ የመጀመሪያ ዝግጅት | EthioTeyim Episode 1
“ጎዳናው እስኪቋጭ” የአሳዬ ደርቤ አዲስ መጽሐፍ
ሽግግሩ ከተከሰተበት ጊዜ አንስቶ በየቀኑ የሚሰሙ ቅስም ሰባሪ ሰበር-ዜናዎች ከመብዛታቸው የተነሳ ለማስታወስ ያዳግታል፡፡ እመርታዎቹ ደግሞ የማይታዩና የማይጨበጡ በመሆናቸው ማይክሮስኮፕ ላይ ተጥዶ ምርምርና ጥናት ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
ከለውጡ ወዲህ የተቀጠፉት ነፍሶች ይሄን ለውጥ ለማምጣት ከተሰውት እየበለጠ ነው፡፡ ይሄም ሆኖ ግን ሰውዬው በምታለቅስ አገር ላይ ፈገግ እንዳለ ቀርቷል፡፡ ሁሉም ነገር የሚሆነው በእሱ ይሁንታ ይመስል፣ በተደናገረው ሕዝብ መሀከል በሁለት ዙር ግንብ ካሳጠረው ቤተ-መንግሥቱ ውስጥ ሆኖ በቃላት ይፈላሰፋል፡፡
*
የመጻፍ ሙዳችን እየመጣ ነው፡፡
ስለምን እንጻፍ? ስለምን እንፈላሰፍ?
“ሽግግር- ከችግር ወደ ችግር” የሚል ርዕስ አስምረን ችግሮቻችንን እንዘርዝር?
ነው ወይስ…
“ለውጥ- ከማጥ ወደ ማጥ” የሚል አጀንዳ ይዘን “እንደ አገር” አብረን እንስመጥ?
ድል- ከትግል ወደ ትግል
ድልድይ- ከገደል ወደ ገደል
ምናምን፣ ምናምን እንበል?
ወይስ?
ለውጡ እንዳይቀለበስ
ትችታችን ጋብ አርገን- ንፋሱን ጋልበን እንንፈስ?
*
እኛን ያላዩ ፈረንጆች-በእውቀት፣ በሀብቱ የታደሉ
“A problem well-stated is a problem half solved” ይላሉ፤
“ሙሉ በሙሉ የታወቀ ችግር በከፊል ምላሽ አግኝቷል” እንደ ማለት፤
ታዲያ የኛ ደዌ እና ተውሳክ- ሙሉ በሙሉ ታውቆ ሳል- እንዴት መፍትሄ ታጣለት?
ለዶክተሩ የነገርነው በሽታችን ሊድን ቀርቶ ስለምን ነው የባሰባት?
መልሱ ቀላል ነው!
በሽታችን ገሃድ ወጥቶ-እንደ ብቅል- ከጸሐይ ላይ ቢነጠፍም
መርፌና ሐኪም ከለገመ- እንኳን ታፋ- ቅቤ አይወጋም፡፡
በሺህ ቃላት ቢቀባቡት- የመርዝ ውህድ- ሽሮፕ ሆኖ አይፈውስም፡፡
በመሆኑም…
ዶክተር በምድሩ ሳለ- ቅስቻችንን ያበረታው- የተያዝነው በጣር፣ ሲቃ
“ሕመማችን ታውቆ ሳለ- መዳኒቱን ተነፍገን ነው” ብዬ ላብቃ፡፡
ትውስታ… (አብደላ ዕዝራ)

መጽሐፍት ሲያዞሩ…

አመፅ ቀስቃሽ ናቸው የተባሉ መጻሕፍት በመሸጥ የተጠረጠሩ አዟሪዎች ታሰሩ
ኅብረተሰቡን ለአመፅ የሚገፋፉና ግጭት ሊፈጥሩ የሚችሉ መጻሕፍት በማዘዋወርና በመሸጥ የተጠረጠሩ መጽሐፍት አዟሪዎች፣ ከነሐሴ 14 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ መታሰራቸው ታወቀ፡፡
ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ መጻሕፍት አዟሪዎች በተለያዩ ፖሊስ ጣቢያዎች መታሰራቸውንና በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ ችሎት ቀርበው ጊዜ ቀጠሮ እንደተጠየቀባቸው ቤተሰቦቻቸው ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
አዟሪዎቹ የተጠረጠሩት ሕዝብ የሚያነሳሱና አመፅ የሚቀሰቅሱ መጣጥፎችን በፍትሕ ጋዜጣ ላይ በማተም ክስ ተመሥርቶበት የሦስት ዓመታት ጽኑ እስራት የተፈረደበት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ በቅርቡ ‹‹የፈራ ይመለስ›› በሚል ርዕስ ያሳተመውን መጽሐፍ፣ ፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ ‹‹የኦሮሞና አማራ የዘር ግንድ›› በሚል ርዕስ ያሳተሙት መጽሐፍና ጋዜጠኛ ሙሉ ቀን ተስፋው ‹‹የዘመኑ ጥፋት›› በሚል ርዕስ ያሳተመውን መጽሐፍ በማዞር ሲሸጡ ስለተገኙ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ጋዜጠኛ ተመስገን ቀደም ብሎ ክስ ተመሥርቶበትና ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ ቅጣት የተጣለበትን መጣጥፍና በድጋሚ በመጽሐፍ መልክ ያሳተመውን መጽሐፍ ማሠራጨት ወንጀል መሆኑን ፖሊስ ለፍርድ ቤት ማስረዳቱ ታውቋል፡፡ ሌሎቹም የተጠቀሱት መጻሕፍት አመፅ ቀስቃሽ መሆናቸውን በመግለጽ መሠራጨታቸው ተገቢ አለመሆኑን ፖሊስ ለፍርድ ቤት አስረድቶ፣ መጻሕፍቱ ሲታተሙ ያተማቸው ማተሚያ ቤት በመጽሐፉ ላይ መግለጽ የነበረባቸው ቢሆንም ሳይገልጹ መቅረታቸውንም አክሏል፡፡ ይኼም ሆን ተብሎ መንግሥት ቁጥጥር እንዳያደርግ በድብቅ የሚሠራ ሕገወጥ ተግባር መሆኑን በማስረዳት፣ ለተጨማሪ ምርመራ ተጨማሪ ጊዜ መጠየቁ ተገልጿል፡፡
የተወሰኑ አዟሪዎች መጻሕፍቶች ተነጥቀው ሁለተኛ እንዳያዞሩ ፈርመው መለቀቃቸውንና ማተሚያ ቤቱን እንዲጠቁሙ ተገደው እንደነበር ተናግረዋል፡፡ ሐሙስ ነሐሴ 18 ቀን 2008 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀርበው ጊዜ ቀጠሮ የተጠየቀባቸው መጻሕፍት አዟሪዎች ሰኞ ነሐሴ 23 ቀን 2008 ዓ.ም. በድጋሚ ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ታውቋል፡፡
የአሜሪካ ድምጽ ሬድዮም ቀድሞ እንዲህ ዘግቦት ነበር…
መጽሐፍ አዟሪዎቹ በተለይ የተመስገን ደሳለኝ፣ የሙሉጌታ ሉሌና የዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ መጽሐፍ መሸጥ እንዳልቻሉ እነዚህን መጽሐፍትና ሌሎች የታሪክና የፖለቲካ መጽሐፍት ይዘው ሲገኙ እንደሚደበደቡ፣ እንደሚታሠሩና አንዳንዴም ለመለቀቅ ከደንብ አስከባሪዎች ጉቦ እንደሚጠየቁ ተናገሩ።