Good news…

Habitamu-Ayalew.jpgThe long waiting and imploring have come to an end, finally! The cruels banned what shouldn’t be banned in the first place, – ‘traveling for better medication’, even traveling for leisure would have been up to the individual… now, they have ‘allowed’ and we’re happy that Habtamu Ayalew is safe in USA. This is an ever ugly drama: ‘they take our rights’, and when they give us back, ‘we celebrate’.

But if one can afford, why not even to the Mars, even to the Moon? What the hell should the government get to do with it? But this is how it is when ‘gun’ governs… it even would have been worse.

Hallelujah! And congrats for all who have been concerned. And all the best Habtish and family!

—-

Habtamu Ayalew, has beenformer spokesman of the opposition, Andenet (Unity), Party, and he was arrested on July 8, 2014 and charged with ‘terrorism for allegedly collaborating with the opposition Ginbot 7’, which the Ethiopian government has proclaimed as ‘a terrorist group’. Habtamu was detained at the notorious Maekelawi and Qilinto Prisons, where he was subjected to torture and other ill-treatment through denial of access to toilet facilities, ‘a situation that led to him to develop excruciatingly painful hemorrhoids’. He was banned from leaving the country because the prosecutor has appealed the ‘release from prison’ decision of the High Court. As known, his hemorrhoids were easily treatable, hadn’t it been left untreated to get worse to stage 3. 

 

 

በአቅመቢስነት :-/

13507048_1604998063164033_3307705846976265661_nቀንቶት የሰው አገር ያየ ግን እንዴት ለአገሩ አይቀናም?? የሰውን አገር ስርዓት የተመለከተ ሰው እንዴት ለአገሩ ያንን አይመኝም?? የሰው አገርን የሰው ልጅ አከባበር ያስተዋለ ሰው ቀጥሎ እንዴት ሰውን ለማዋረድ (በዚያም ራሱን ለማዋረድ) ይፈቅዳል?? ባለስልጣናቱ በየስብሰባው፣ በየሽርሽሩ እና በየሰበብአስባቡ፣ በየተረተሩና ሸንተረሩ ሲንቀዋለሉ፥ እንዴት ነው… መንገዱን፣ ጽዳቱን፣ ስርዓቱን፣ ልምላሜውን፣ ጥጋቡን፣ ቅንነቱን፣ ሌላ ሌላ መልካሙን ሁሉ አገር ቤት ጭነው ስለመሄድ የማይቋምጡት??
 
ይገርማል! ሰው አገር ውስጥ ሰው ቢታመም፥ አስፈላጊውን ህክምና ከሰጡ በኋላ ነው ስለቢል የሚያወሩት፤ እንጂ ነፍስ ውጪ ግቢ የሚልን ሰው ህክምና አይነፍጉም። ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በሰፈነባቸው አገራት፥ ፍትህ ይከበር ዘንድ፥ በወንጀል የሚፈለግ ሰው እንኳን እንደዋዛ በሞት ሲሰናበት ይበግናሉ። ቢችሉ አስታመው፣ አሻሽተው ነው ለፍትህ የሚያቀርቡት። (አሁን ለምሳሌ፥ ይሄን ሁሉ ነቀርሳ የተከሉት የቀድሞው ጠ/ሚ ሞት ልብ ተብሎ፣ በንጹህ አእምሮ ቢታሰብ እንዴት ያበግናል? እንዲሁ እንደጻድቅ ማሸለባቸው ሲታሰብ እንዴት ያንገበግባል? መቼስ ነፍስ የእግዚአብሔር ነውና ከሞት በኋላ አይፋረዱ ነገር!)
 
እነሱ ስለመንገድ እንጂ ስለተራማጅ ሰው ማውራት እርማቸው ነው። ስለህንጻ እንጂ ስለሰውነት መባዘን ሞታቸው ነው። …እንደው ህንጻና መንገዱንም በቅጡ በሰሩት እኮ! ሰው አገር ያለውን የመንገድ ስርዓት በቀዱት! ለፓርኪንግ (ለዚሁ ብቻ በታነጹ) ስንትና ስንት የተንጣለሉ ህንጻዎች ውስጥ ተሹሎክሉኮ መኪናውን ያቆመ ባለስልጣን፥ አገሩ ላይ ስለልማት ሲያወራ እንኳን፣ ጥራት እና ደረጃ እንኳን ህቅ አያደርገውም? “ልማት ልማት፣ እትት ብትት፣ ጸረ ልማት ኃይሎች…” ሲገርም! ሲያሳፍር!
 
“ኮንዶሚነም ተሰራ” ቢባል፥ ግማሹ በዝምድና እና በፖለቲካ ተሳትፎ ተደልድሎ የተረፈው፣ በስንትና ስንት ስለት እና ጾም ጸሎት በሚደርስ ዕጣ እንኳን፥ “ፈረሰ አልፈረሰ”፣ ሌት ተቀን በስጋት ነው። ደግሞ ሰው ስብሰባ ጠርቶ፣ ሰው አገር የታለፈ እና፣ ሌላ ሰው እንዲያነሳው በክብር የትም የሚጣል ጥሪት (ኩርሲ፣ ጠረጴዛ፣ መሶብ፣ ሶፋ፣ ብፌ፣ ቴሌቪዥን፣ አልጋ፣ መደርደሪያ፣ ሌላም ሌላም… ) ላይ ቤት መናድም አለ። የከርታታን ሰው፥ ተስፋንም፣ ጉጉትንም፣ ጥረትንም አብሮ መቅበር አለ። ከዚያ ሰላማዊን ሰው አውሬ ማድረግ! “ምን ልብላ” ብሎ ሥራ ሲፈልግ፥ ፈርዶበት አግኝቶት ለመንግስት ያፈነደደንና ሆዱን ለመጠቅጠቅ ሰፊውን ህዝብ በከንቱ ያስለቀሰ እና ያስቀመየን ምስኪን ፖሊስ ማስበላትና ደሙን በከንቱ ማፍሰስ! :-/
 
ከዚያ፥
 
“ሳሩን በልቶ ውሀውን ጠጥቶ የተኛውን በሬ፣
ጎትጉተው ጎትጉተው አደረጉት አውሬ” ይዘፈናል።
 
አንድን በሀሳብ የሚሞግት ተቃዋሚን ሰው፣ እሱንም በሀሰት ወንጅለው እንደማይገባው በግፍ ያንገላቱትን፣ ለህክምና እንዳይጓዝ በማገድ ማሰቃየት ክፋት እንጂ ሌላ ምን ይሆናል?? ከአገር ቢወጣ ምን እንዳይጎዳቸው ነው?? መቼስ አገር ውስጥ ሆኖ ከእንግዲህ ድኖ ለእነርሱ ሰው አይሆናቸው። ወጥቶ እንዳይቀር ሰጉ?? ምነው ይሄን ያህል፥ ሺህ ዓመት አይኖር! ሺህ ዓመት በድለው እና አሳቅቀው አይነግሱ! በየትኛውም አገር ታሪክ ከዚህ ቀደም ሲበድሉ የነበሩት ቀናቸው ሲደርስ ከቅጣት አለፉ??
 
ወዳጄ ሀብታሙ አያሌው የምታምነው አምላክ ይቅደምልህና በምህረቱ ይጎብኝህ! ቅድስት ማርያም ትዳብስህ! ልባቸውን ያራራልህና ወጣትነትህ ለቤተሰብህና ለህልምህ ይትረፍ!