“ዘፈን” በመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜዎች ውስጥ! – ሠርፀ ፍሬስብሐት | “ኢትዮጵያ” መሠረት ክንፈ | Ethio Teyim | Episode 29

“ዐይኔ ዓለም አየ”፤ የላሊበላ ልጅነት እና የቦታ ፍልስፍና (አጭር ቆይታ ከዶ/ር ይርጋ ገላው ጋር) | Ethio Teyim | Episode 14

“ሄዋን እንደዋዛ”

“ሄዋን እንደዋዛ ፍሬዋን በልተሽ
በእኔና በምድር፣ ሞት እንዳመጣሽ”
 
የሚላት የመጀመሪያዋን ቀዳማዊት ሄዋን ነው
 
“ለባከነው ልቤ ራርቶ ልብሽ
መጽናናያ ሆኖኛል፣ ክሶኛል ፍቅርሽ”
 
ሲል ደግሞ ይኽቺ ዳግማዊት ሄዋን እመቤታችን ማርያም ሆና፣ በልጇ በክርስቶስ እንደካሰችን ነው የሚያሳየው።
 
~ ቴዲ አፍሮ ❤
 
“ልቤም ተደላደለ ጎኔም ደላው መሰለኝ
አንቺን ስለመውደዴ፣ አገር ሰምቶ ጉድ ቢለኝ
ከወደድኩሽ ወዲያ ምንድን ነው?
ቢጠፋም ስሜ ነው።
በዚህች ዓለም ስኖር ሰው ነበር ረሀቤ
ምኞቴ ተሳካ ባንቺ አረፈ ልቤ…”
 
እያለ ነው እንግዲህ ዘፈኑ ጀምሮ……….
 
“ሄዋን እንደዋዛ ፍሬዋን በልተሽ
በእኔና በምድር፣ ሞት እንዳመጣሽ
ለባከነው ልቤ ራርቶ ልብሽ
መጽናናያ ሆኖኛል፣ ክሶኛል ፍቅርሽ”
 
የሚለው ጋ የሚደርሰው። እንዲህ ቅልጥ ባለ እና ቅልጥ በሚያደርግ የፍቅር ዘፈን ላይ፥ ይኼ ማርያምን ነው የሚገልጸው ማለት ለምን እንደሚጠቅም አላውቅም። አንዳንዱ ነገር ባይብራራ ሳይሻል አይቀርም።
* * *
ጎሳዬ ተስፋዬ ❤ “እናትዬ የሚለውን ለማን ነው የዘፈንከው?” ሲባል
 
“ለእናቴ” አለ ብለው ሲያነፍሩን ነበር። (ቃለ መጠይቁን አልሰማሁትም) እንግዲህ “ሁለት እናት አለኝ…” ሁሉ የሚል ሀረግ አለው። 🙂
 
እንግዲህ “አቤት ብቻ ነው ሲጣሩ እቴጌ!” ተብሏልና፥ የምንወዳቸው ከያንያን ሲሉን፣ አሉን ነው። 😉
* * *
የስዕል አውደ ርዕይ ልንመለከት ሄደን ሙንጭርጭር ያለ ስዕል እናይና፥ ቀለሙን ብቻ ወደነው እንኳን እንዳናልፍ ለነገር ሰዓሊው እዚያው ቆሞ እናገኘዋለን። …ዐይን ዐይኑን እያየን ትርጉሙን ከፊቱ ላይ ልንፈልግ ስናፈጥ፥ ማስረዳት ይቀጥላል።
 
“…እዚህ ላይ ቀዩ መስመር ህልማችንን ነው የሚወክለው። ወደዚያ የሄደው ሰማያዊ ደግሞ… ጥቁሩ መደራረቡ የሰዉን የኑሮ ውጣ ውረድ… እዚህ ጋ ደግሞ አይታይም እንጂ፣ ጽጌረዳ አበባው መድረቁ ህልም የመሰለችኝ ፍቅሬ ትታኝ መሄዷ…”
 
“አሃ” እያልን፣ ራሳችንን በአዎንታ እየነቀነቅን፣ በልባችን “ወንድሜ እኔ የማየው ነገር የለም” እንላለን።
 
የባሰም አለ፥ “ወንድም ይኽ ስዕል ምን ለማሳየት ነው?” ሲባል
 
“አይ ለራሴ ነው የሳልኩት”
 
ምንሼ አደባባይ ማውጣቱ?
.
.
እመው “ተከድኖ ይብሰል” ይሉትን ፈሊጣዊ አነጋገር ካለነገር አላሉትምና! አንዳንዱ ነገር ባይብራራ እና ከተሰራ በኋላ በመጣ እውቀት ለመቃኘት ባይሞከር እንዴት ሸጋ ነበር?!
 
ሰላም! 

Adey/አደይ

The fusion of Paul Simon’s ‘Under African Sky’ with ትግርኛ (Tigirigna) beat, in a lyrical theme of recounting mothers in mother land (Ethiopia) and the other way round, is priceless. I am listening it on repeat. Plus, as tomorrow is #mothersday, herewith, I would like to invite you join in my cd-concert 🙂
 
Our mothers are kingdoms of our joys, queens of our lives, and crowns of our lifetime triumphs. As Marcus Garvey express mothers on his poem ‘The Black Women’ (he either, recounting them with in mother continent (Africa), they are our “black queen of beauty; goddess of Africa, nature’s purest emblem”. It is long rooted that we relate our mothers with our mother land.
 
So, when we say ‘happy mother’s day’, we also mean ‘happy mother land’ that we all deserve to see a place where people of the world can live happy, as everything has been safe in our mothers’ embrace. We all should defend humanity! We all should say ‘NO’ to inhumanity!
10311933_565603356894035_3772060369240297996_n
“ከአፍሪካ ሰማይ ስር
እናቴ ስትወልጅኝ ገና
ዓይንሽን ሳይ
በማይለካ ፍቅር ወደሽኝ
ራስሽን ሰጠሽኝ፣ ጡትሽን
 
በችግር ተነክረሽ
በድህነት ጸሐይ ጠቁረሽ
አሳደግሽኝ
ሰው አደረግሽኝ
 
እናቴ እናቴ
እናቴ… እልሻለሁ
የፍቅር አገር፣ ቤቴ፤”
 
Happy Mother’s Day to all mothers! Happy Sunday!
 
#Ethiopia #mamaEthiopia #mamaAfrica #mamaWorld #TeddyAfro #PaulSimone #MarcusGarvey #TheBlackWoman #UnderAfricanSky
 

To the king!

He came to earth 71 years ago, on this day; and died when he was only 36. As if ‘effectiveness’ means his life, he lived it well tho. And he is living in us forever. I wonder, how boring would life be, hadn’t it been for me to learn about music, him and his kinds?
 
Whenever I recall the goodness of life and the jewels; the hopes that everything will be alright, and the joys in my life; or whenever I feel achieved and acquainted with new things, or being on the right track towards conscience, passions and career, my heart looks like this face of him 🙂
tumblr_static_tumblr_static__640
Happy birthday the king, the one and only, Bob Marley
 
I will always love you!

‘በከበረች ሰንበት’

ሙዚቃ አሁንም እየፆምን ነው። የስራውን ይስጠው፥ መብራት ኃይል ከሙዚቃ የተፋታ በዓል እንድናሳልፍ አድርጎናል። ሞባይሎቻችን ያቆሩትን ኃይል እስኪያሟጥጡ ድረስ ሬድዮ ያመጣውን ሙዚቃ ሁሉ ተቀብለው ወደ ጆሮዎቻችን እንዲያሳልጡ ፈቅደንላቸው ነበር። …ነበር። (ለመነጋገሪያ የሚጠቅሙን እንደው እንደ እድል ነው። በዓመት በዓል ደግሞ ይብስባቸዋል። ዛሬ ወንድሜ “Merry Christmas” የሚል የፅሁፍ መልእክት ደርሶት ስንስቅ ነበር። ግን የቴሌ ነገር ስለማይታወቅ ያን ያህል አያስቅም።) …ይብላኝ ለእነሱ እንጂ፥ ለበዓል የቤተሰብ ጫጫታ ሙዚቃ ነው። የዓመት በዓል ድባቡ ራሱ ድምፃም ሙዚቃ ነው። ቀጤማውና ጭሳጭሱም ይዘምራሉ። …ዋዜማውን እንደው ዶሮና በጉ ያደምቁታል።
 
ያው ትናንት እንዳጫወትዃችሁ፥ ነፍሴን ካወቅኹኝ ጊዜ ጀምሮ፥ ከአንድ ጊዜ በቀር፥ ለፋሲካ በዓል መብራት በርቶልን አያውቅም። ….በዋዜማው ከጠዋት ጀምሮ ሌሊቱንም ጠፍቶ ያድርና እሁድ ይከሰት ነበር። መብራቱ! ”እንኳን አደረሳችሁ“ የሚል ዘመድ ይመስል ድንገት ብቅ ይልና የሁላችንም ገፅ ላይ ፈገግታ ይዘራል። በሰው አምሳል ሆኖ ያፌዝብን ይመስለኝ ነበር።
 
እኛም ወስደው ሲያመጡት እናመሰግናቸዋለን። “እሰይ!ኧረ እግዜር ይስጣቸው” ትላለች እናቴ። እንደ ትናንት የነሱንን አስታውሶ ሊራገም የሚያስብ ካለ፥ አይዘልቀውም… እናቴ “ሁሉ በእጃቸው አይደል? አሁንስ ቢከለክሉን ምን እናመጣ ነበር? ዝም ወሄ!” ስትል ያቋርጠዋል፥ (ዝም ወሄ፥ በጉራጊኛ “ይህም መልካም ነው” እንደማለት ነው።)
 
መብራት ማግኘት እንደውመብታችን ሳይሆን የመብራት ኃይል ፈቃድ መሆኑን በደንብ ተገንዝበን ለምደነዋልና ብንንጨረጨርም ለአመላችን ነው። ለያውም በአፍታ የሚረሳ መንጨርጨር። ኤሌክትሪክ ይዞ እንደሚያንጨረጭር ዓይነት መንጨርጨር። ….ባለፈው፥ አንድ ጉብል የመኝታ ቤቱን ሶኬት አስተካክላለው ሲል መብራት ይዞት ሞቶ ተገኘ ተባለ። እንዲህ ነን!መድኃኒት የተቀመጠበትን ቦታ ለማየት ጭላጩ የጠፋ መብራት፥ የሰው ነፍስ ለመቅጠፍ ደራሽ ሆኖ ይመጣል።
 
የዛሬው ግን የተለየ ነው። በከፊል ነው የጠፋው… ትይዩ ካለው ሰፈር አለ። ትናንት ጠዋት የጠፋ እስካሁን አልመጣም። “እንኳን አደረሳችሁ” አላለንም። …ጭራሽ ቅርብ ሰፈር መብራት እየታየ በከፊል መጥፋቱ “ከእኛ ጋር ምን አላቸው?” ያሰኛል። አንድ ጓደኛዬ ደውሎ፥ ስንጫወት “ከምርጫ ጋር በተያያዘ ቂም አስቋጥራችሁ እንዳይሆን” ብሎ አሾፈብኝ። አብረን ሳቅን። ቻዎ ሳንባባል ስልኩ ተቋረጠ። ይህንንም ለምደነዋል። ኔትዎርኩ ነው! …ደግነቱ በጨዋታ መሀል ካልሆነ በቀር ማን ያስታውሳቸዋል? እንዲህ ሲጨላልም፣ ፀሐይቱ ቻዎ ስትል ግን መብራት ግድ ይታወሳል።
 
“ወይኔ… እንዲህ ይቀልዱብን?” ትላለች የጎረቤት ሰራተኛ።
 
“ምን ታረጊዋለሽ?” ሌላዋ ትቀጥላለች። (በራፍ ላይ ተገትረው ነው የሚያወሩት)
 
“ተስፋ መቁረጥ ነው ባክሽ! እንዲህ ለይተው ከወሰዱት አይመልሱትም። ከ3 ቀን በኋላ ስንረሳው ይመጣል።”
 
“ጊዜው በእጅ መሄጃ፥ እኛ የምንሄደው በእግር። ምን ያድርጉ?”
 
“ማለት?”
 
“ስልክ እንጨቱ ላይ የሚያስተካክሉት ነገር አለ። እንዲህ ተከፋፍሎ የሚሄድባቸውን ሳንቲም ተቀብለው ያስተካክላሉ እኮ”
 
“እውነትሽን ነው?”
 
“አዎ! ታች ሰፈር እንደዛ ነው ያስተካከሉት። አሉ”
 
“ስንት ከፈሉ?”
 
“150፣ 200 ቢሰጣቸው ያስተካክሉታል።”
 
ስለ አሰጣጡ ማውራት ቀጠሉ
 
አሰጣጥ….
 
በምክንያት (ከዚህ ቀደም “ፋሲካ” በሚል ርዕስ የለጠፍኩትን ለመተየብ) ይዤው ሳላስብ ማንበብ (ከመሀል መገረብ) የቀጠልኩትን “ግራጫ ቃጭሎች” መፅሐፍ እያነበብኩ ነው የምሰማቸው። ወንድሞቼ ደግሞ እንድንወጣ ያዋክቡኛል። (እግረ መንገዳችንን የሙዚቃውን ፆም ለአፍታ እንገድፋለን።)
 
“ቆይ አንዴ… ይህችን ላንብብ….”
 
“ኧረ ፋሲካ ነው!”
 
“አንቀፁም የፍስክ ነው ኧረ ።”
 
ተሳሳቅንና አነበብኩላቸው….
 
—–
“ዋናው አሰጣጥሽ ነው።” አልኳት።
በዚህ አባባሌ ቤቱ ውስጥ የነበሩ ጥቂት ሰዎች በሙሉ በሳቅ አይፈነዱም! ጫልቱ ራስዋ አፍዋን ወደ ሰማይ ሰቅላ ተንካካች። እየሳቁ፣ እያረፉ ደ’ሞ የተናገርኩትን ቃል እየደጋገሙ:….
“አሰጣጥሽ አላ !”
“ሆሆይ… አሰጣጥ! እ?”
“አሃ…. የት ትተዋወቃላችሁ?!”
በቃ የመሳሰለ የሚያበሽቅ ነገር መናገር ጀመሩ። ምን ለማለት እንደፈለግሁ እንዳልገባቸው ሁሉ ዕንባ ባቀረሩ ዐይኖቻቸው።
(ለመሆኑ ዕንባ የሚያስቀርር ምን ነገር ተናግሬ ነበር?)
 
[አዳም ረታ (1997) “ግራጫ ቃጭሎች” ገፅ 148]
—–
ሴቶቹ ስለ 150 እና 200 ብር አሰጣጥ አውርተው ጨርሰዋል። (አልሰማዃቸውም)
 
“ውኃውን መልቀቃቸው ግን ደስ አይልም?“ አለች ሴትዮዋ። ወሬው ጥሟት እንዳትገባባት መያዟ ይመስላል።
 
“ኧረ ባይለቁት ይሻል ነበር። ክንዳችን እስኪገነጠል፣ የትናየት ሄደን ቀድተን ካጠራቀምን በኋላ…” አለች ተበሳጭታ። (‘አንቺ አትቀጂ ምናለብሽ? እንደኛ ሞክረሽው ስቃዩን ብታውቂ ኖሮ ለመንግስት አቤት ትዪ ነበር’ የምትልም ይመስላል።
 
“ሆ… እውነትሽን ነው እኮ። እኛን ማቃጠል ነው ግን ስራቸው?”
 
“ስታዪው! በይ አፌን አታስለቅሚኝ።”
 
ማፅናኛ ይመስል ውኀው ተለቆልናል። እኛም ብርቅ ሆኖብን ውኃውን እየደጋገምን ነው። – ለናፍቆቱም። ለማቆሩም። ለምኑም። ለመርሳቱም። …መጠጣት ጥሩ ነው። ደግሞ ውኀ ስንፆም ነበር። ማለቴ ከቧንቧ እንደወረደ ውኀ መጠጣት ስንፆም ነበር። ይኸው ዛሬ ከቧንቧ ውኀ ቀድቶ በመጠጣት ፆማችንን ገደፍን።
 
መብራት ግን እየፆምን ነው። በፊትም አመጣጡ በፆም መሀል እንደማፍረስ ዓይነት ‘ብቅ’ ነበር። መብራቱ ብቅ ይልና ከብርሃን ፆማችን አፋርሶን እልም ይላል።
 
ልቤ ግን ይህን ትዘምራለች…
 
“በከበረች ሰንበትበአምላክ ትንሳኤ፥
ሰላም ተሰበከ በመላው ጉባኤ!
በመላው ጉባኤ በመላው ዓለም
የሰው ልጅ ተፈትቶ ታሰረ ሰይጣን!”
 
እንደመፈታታችን፥ ስርዓት ባለው ነፃነት የምንኖር ያድርገንማ!በድጋሚ መልካም የትንሳኤ በዓል ለምታከብሩት ክርስቲያን ወዳጆቼ ሁሉ!