የሁለት ፕሮፌሰሮች ወግ…

 “ከቤተሰቤ መካከል አማርኛ የምችል እኔ ብቻ ነኝ።mqdefault
ሌሎች 13 ወንድምና እህቶቼ አማርኛን እንዳይሰሙም
እንዳይናገሩም አድርገን በጥሩ ሁኔታ አሳድገናቸዋል።
አሁን ያለዉ የቁቤ ትዉልድም ከሞላ ጎደል አማርኛን
የማይናገር የማይሰማ ጀግና ትዉልድ ሆኗል።”

~ ፕ/ር ህዝቅኤል ጋቢሳ (በOMN)

merera-gudina100

“ቋንቋን በአግባቡ ያለመጠቀም የኦሮሞ ሕዝብ ተገቢ የመብት ጥያቄዎችን ለሌሎች እንዳያስረዳ እንቅፋት ከሆኑበት ነገሮች አንዱ ይመስለኛል፡፡ በ1983ቱ የሽግግር ጉባዔ ላይ እነ ኦቦ ሌንጮ ለታ ለየት ለማት በአስተርጓሚ ለመናገር ሲሞክሩ፣ አቶ መለስ በመንዝአማርኛ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ሲፈልጥና ቆርጦ ሲቀጥል ነበር፡፡ ፓለቲካ ለሚያውቅና ለገባው ሰው፣ ኦሮሚፋ አንድ ቀን እንኳ በአደባባይ ይሰማልን የሚባል የአናሳ ቡድን ቋንቋ ሳይሆን ትልቁ የኢትዮጵያ ብሄር የሚናገረው ቋንቋ ነው፡፡ ሙዚየም ውስጥ ይቀርብኛል ተብሎ የሚሰጋለት ቋንቋ አይደለም፡፡ የቋንቋ ፖለቲካ የማይናቅ ባይሆንም፣ በተገቢው ጊዜና ቦታ ካልተጠቀሙ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ሊያመዝን ይችላል፡፡”

~ ፕ/ር መረራ ጉዲና – “የኢትዮጵያ ፓለቲካ ምስቅልቅል ጉዞና የሕይወቴ ትዝታዎች ከኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ እስከ ኢህአዲግ” ገፅ 225

ቋንቋ

መግባቢያ ነው። ክህሎት እንጂ እውቀት አይደለምና ባይችሉ አያሳፍርም። መቻሉም ቢያስደንቅና ቢጠቅም እንጂ፥ የተለየ ሆኖ የሚያስኮፍስ ነገር አይደለም። ሰው እንደዋለበትና እንደፈለገው ልክ የትኛውንም ቋንቋ ማወቅና በአግባቡ የመጠቀም ክህሎቱን ማሻሻል ይችላል። ብዙ ቋንቋ ባወቀ ቁጥር ግን የተሻለ መግባባት እና መፍትሄ ማምጣት ይችላል።

በተለይ፥ ቋንቋውን ሆነ ብሎ ላለመማር መጣርም ጉልበትና ጥረት ይጠይቃልና ራሱን የቻለ ድካም አለው። ማለዳ ማለዳ ተነስቶ፥ ልጆችን ስለጥላቻ መስበክ፣ እሱን ቋንቋ እንዳትናገሩ ብሎ መጨቆን፣ ጓደኞቻቸውን መምረጥ፣ ውሏቸው ላይ ጣልቃ መግባት… ሁሉ የመብት ጥሰቶች ሆነው ያስወቅሳሉ እንጂ፥ እንደጥሩ ገሪነት የሚያስደንቁ አይደሉም። ወላጅ/አሳዳጊ ከዚህ በላይ ሊበድልም አይችልም!

እኔ ኦሮሚኛ ለመማር ከምደክመው በላይ (አዲስ ቃል ብሰማ እና አፌ ውስጥ ቢገባ ለመጠቀም እደጋግመዋለሁ እንጂ ስለመርሳት አልጨነቅም) እነ ፕሮፌር እዝቅሔል ቤተሰብ ልጆቻቸው አማርኛ እንዳያውቁ የደከሙት ሲታሰብ ያስቆጫል። ልጆች ከሰው ጋር ተግባብተው እንዳይኖሩ መፍረድ ኅሊና ላለው ሰው ግፍ ነው።

በክልልስ እሺ፥ መንግስትም ለይስሙላ ፌደራሊዝሙ ሲል “በአፍ መፍቻ ቋንቋ አስተምራለሁ” ይላልና በዚያ ያልፋሉ። 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሲመጡ መግባባት ከባድ ይሆናል። ዩኒቨርስቲ ሲገቡም እንዲሁ ሆኖ ሰው ባያገል እንኳን ራስን ማሸሽም ይከሰታል። ሕብረተሰብ ካልተግባባ ደግሞ ግፈኞች ጥሩ ምሽግ ያገኛሉ።

ስለታሪክስ ቢሆን በአንድ ቋንቋ እና ወገን ብቻ የተነገረውን፣ እንደዶግማ ከመጋት፣ ብዙ ማስረጃዎች (resources) ያሉበትን ቋንቋ፥ “ላስተምር” ብሎ መጣር ቢቀር፣ “እንዳይማሩ” ብሎ መነሳት ክፋት እንጂ ሌላ ምን ምክንያት አለው?

በአሜሪካ

20160709_200649ፕሮፌሰሩ እዝቅሔል ገቢሳ፣ ካለክልሉ አስጠግታው፣ ቤት ንብረት አፍርቶ፣ “ሰዎችን ከክልላችን ውጡ” እያለ እንደልቡ እየተከፈተ በሚኖርባት እና በሚያስተምርባት አገረ አሜሪካ…

ሰሞኑን የሜሪላንድ የጤና መድኅን ዋስትና ማዕከል፣ ለደንበኞቹ የላከው ደብዳቤ ላይ ወደ 17 የሚጠጉ ቋንቋዎች (Bassa የሚባል ስሙን ሰምቼው የማላውቀው እና፣ ‘Khmer’ እና ‘Laotian’ የሚባሉ ቋንቋዎች፥ ፊደሎቻቸው እርስበርስ ተያይዘው ሸረሪት ቀለም ነክታ ወረቀቱ ላይ የሄደችበት መስለው የሚያስቁ ሳይቀሩ ተካተው) ተጠቅሞ ያስተላለፈውን መረጃ ተመልክቼ ነበር። ከቋንቋዎቹ ውስጥ፥ አማርኛ እና ኦሮሚኛም ተካተውበታል።

በአማርኛ የተጻፈው….

“ያለምንም ክፍያ በራስዎ ቋንቋ እገዛ የማግኘት መብት አለዎት። ስለማመልከቻዎ ወይም ከጤና ዋስትና ድርጅቱ ስለሚያገኙት ሽፋን ማንኛውም ጥያቄዎች ካሉዎት፣ ወይም ይህ ማሳወቂያ በግልፅ በተጠቀሰ ቀን ማድረግ ያለብዎ ነገር እንዳለ የሚያስገድድዎ ከሆነ፣ በተጠቀሰው የስልክ ቁጥር ለስትቴትዎ ወይም ለክልልዎ ደውለው ከአስተርጓሚ ጋር ይነጋገሩ።” ይላል።

20160813_193553አሜሪካ ውስጥ፣ ከቆሻሻ መጣያ ቅርጫቶች አንስቶ በተለያዩ ቦታዎች፥ የአማርኛንም ሆነ ሌሎች ቋንቋዎችን ተጠቅመው ለመግባባት ሲጥሩ ይታያል። በሂደቱ፥ የሚያስቁ አጠቃቀሞችም አይጠፉም።

ከገጠሙኝ መሀል፣ በ’ዋሽንግተን ኤቲካል ሶሳይቲ’ አዳራሽ መጸዳጃ ቤት ግድግዳ ላይ “Do not put paper towels in the toilets.” የሚለውን መልእክት በ5 የተለያዩ ቋንቋዎች ለማስተላለፍ ሙከራ ተደርጓል። በአማርኛ የተጻፈውን ስመለከተው፥ “ዶ ኖት ፑት ፓፐር ቶወልስ እን ቶእለፅ!” ይላል። 🙂

ስንት አለ ቶእለፅ ራስ አቦ!? …ሳይሾም የነገሰ፣ “እሟገትልሃለሁ” የሚለውን ኅብረተሰብ ሳያውቅ የሚንቧቸር የእንግዴ ልጅ!

ሲደፈርስ!

ትግሉ መስመር እስኪይዝ ድረስ፥ እንኳን በኢትዮጵያ አንድነት ከሚያምኑ ኦሮሞዎች ጋር መስማማት ቀርቶ፥ የአማራ እና የኦሮሞ ዛፍነትና የስሮቻቸው ተጨባባጭነትም ይቀነቀናል። እስከዚያ፥ ተመልካች (audience) እየለዩ፥ ዓላማን ለመሸፋፈን እና ወቅታዊ ተቀባይነትን ለማግኘት፥ በየቋንቋው የተለያየ ነገር ያስተላልፋሉ። ስጋቱን ለመግለጽ የሚሞክር ቢኖር፥ በ“ትግል አታዳክም” ታፔላ ሊሸማቀቅ ይዳከራል። ትግሉ መስመሩ ተጠናክሮ ዳር ሊይዝ አጥቢያው ሲመስል ደግሞ፥ “አገር ይፍረስ! እንክትክቱ ይውጣ!” ይባላል።
 
ይገርመኛል! ፊደል መቁጠር ለዚህ ለዚህ ካልጠቀመ ለምን ሊጠቅም ነው? በተለይ በባዕድ አገር ላይ፥ “ከየት ነህ? ማን ነህ? ምን ቋንቋ ትናገራለህ? ለምን መጣህ?” ሳይባል፣ ተመቻችቶለት እንደልቡ እየኖረ እና እንደ ኅብረተሰቡ አካል ተመሳስሎ እየተማረ፣ በሞያው እያገለገለ፣ መብቱን አስከብሮ ሸጦ ለውጦ እየተዳደረ፣ ቢሻው ሀብት ንብረት እያፈራ እና ቋሚ እሴት እያጠራቀመ፥ እንዴት ለገዛ ወገኑ እልቂት መፈራረስን ይመኛል? በእንግድነት በተድላ ከሚኖርበት ቦታ እንኳን እንዴት ይህንን ትምህርት አልቀሰመም? እንዴት በመከራ ውስጥ ሆኖ ነጻነቱን ሲፈልግ፥ ባልጠገበ አንጀቱ በአምባገነን ስርዓት ወድቆ የቀረ ወገኑ ደም ላይ ይሳለቃል?
 
ይኽስ ማንን ይጠቅማል? ሰድቦ ለሰዳቢ አሳልፎ ለመስጠት ካልሆነ፥ ማንን ወደፊት ያራምዳል? እስከመቼስ በአንድነት እና በትብብር አብሮ የሚኖረው ሕዝብ፣ በሆዳም ‘አዋቂ’ ነን ባይ ፖለቲከኞች “አይ አብረህ መኖር አትችልም” ይባልለታል? ለእነሱ አገር በማፍረስ ዋጋም ቢሆን የሚገኝ የስልጣን ጥማት ማርኪያነት ለምን ይናፈቃል? ትናንት የመጡትስ ከዚህ መች ተለይተው ጀመሩት? ደግሞ፥ “ይሁን” ቢባልና ቢሳካስ በሰላም መኖር ይቻል ይመስላቸዋል? ወይስ በቃ አገሪቱን ተቃርጠው በየክልሉ ተመሳፍነው ሊያስገብሩ ነው?
 
እንዲህ ዓይነቱ ጨዋታ፥ የሴረኞችን ህልም ከማሳካት ይልቅ፥ ሙሉ አገሩ ስለአንድነቱ በጋራ እንዲቆም እንደተላለፈ ጥሪ የሚቆጠር ነው። አገራችን በጨካኝ ስርዓት እጅ ባለችበት በዚህ ሰዓት፥ ‘አገር አፍራሽ ሆነን፣ ልንበትንህ መጥተናል። እኛ መሲህ ነን’ ዓይነት ነጋሪት ብትጎስሙበትና ከያዘው ትግል ልታጓትቱት ብትጥሩ፥ አይምራችሁ! የነጭ ስልጣኔ፣ ገንዘብና የተሻለ ኑሮ ሳያጓጓቸው በባዶ እግር እና በጨበጣ ውጊያ ጣሊያንን እንኳን ገርፎ የመለሰ ሕዝብ አገር ሰዎች ነንና መቼም አይሳካላችሁም!
 
መተዋወቅ ያስፈልጋል። ስለማታውቁት፣ ወይም ድሮ አውቃችሁት ስለረሳችሁት ሕዝብ ነው የምትደሰኩሩት። “ዶሮ ብታልም ጥሬዋን” እንዲሉ፥ መከራ የፈነቀለውን እና በጋራ የቆመውን ሕዝብ “የኔ ጦር ነው…የኔ” ትባባሉበታላችሁ። ቢቆስል፥ ‘የውሻ ቁስል ያድርግልህ’ ያላላችሁትን፣ ቢሞትበት፥ የቤተሰቡን ትኩስ አስከሬን ፎቶ በየገጹ ከመቀባበል ያላላፈ፥ ጠንከር ያለ “ነፍስ ይማር” እንኳን ያላላችሁለትን፥ ደሙን ገብሮ ነጻነቱን ለመቀዳጀት ደፋ ቀና ሲል… ‘እኛ ነበርን እግዚአብሔሮችህ፣ ከኋላህ ቆመን በለው በለው ስንልህ የነበርን። አሁን ድል አገናኝቶን የባንዲራህን ጨርቅ አስቀድደን፣ ልንሰቅልልህና ልናሸጋግርህ መጥተናል’ ብትሉት አይሰማችሁም። ኢህአዴግም በብዙ ነገር ከፋፍሎ፣ በትንሽ ትንሹ ጠርንፎ፣ በሀውልትና በፕሮፖጋንዳ፣ ‘በታትኜ ያዝኩት’ ያለው ሕዝብ፥ አንድ ሆኖ እያስደነበረው ነው።
 
አሰቃቂው የኢሬቻ እልቂት ሳይቀር እንኳን፥ እንደጥሩ ትግል ማቀጣጠያ ቤንዚንነት ያስደሰታችሁና፣ እንደ ጥብስ ወሬ ያነቃቃችሁ፥ “የአገር መፍረስ ህልመኞች” እንዳላችሁ ልባችሁ የሚያውቅ ታውቁታላችሁ። ቱኒዚያ ቦአዚዝ ራሱን ቢለኩስ፥ ቤንዚን ሆኖ የነጻነት መንገድ እንደጠረገላቸው፣ ለግብጽ አብዮትም የካሊድ ሰይድ ግፈኛ አገዳደል እርሾ ሆኖ እንዳሰባሰባቸው፥ ሰው በሞተ ቁጥር ህልማችሁን የማሳካት ሴራችሁ ከግብ እንደተቃረበ በመቁጠር ብቻ… በመሰባሰብ ፈንታ፣ ‘የድል ዋዜማ ላይ ነንና ብቻችንን እንቁም’ በሚል ብልጣብልጥነት ስንቱን ለማግለል እንደጣራችሁም፣ ስንቴ በጠላት እንዳሳለቃችሁብን የምታውቁ ታውቁታላችሁ። ኦሮሞ ያልሆነ ሰው የኦሮሞ ፖለቲካ ላይ ሀሳብ ቢሰጥ፥ በ’oromophobia’ ፈርጃችሁት፣ ፍርሀትን ለመትከል የለፋችሁም ታውቁታላችሁ።
 
“እንለይህ” የምትሉት ወገን፥ በጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ እንኳን አንድ ቦታ የተከማቸ፣ ባህሉንም ያልተወራረሰ አይደለም። እንለይህ የምትሉት ወገን፥ እንጀራ ተበዳድሮ እና ሚጥሚጣ ተዋውሶ፣ ለቡና እየተጠራራ፣ ልጁን እርስ በርስ እየተቀጣጣ፣ ቤቱን ቁልፍ አልባ ትቶት “መጣሁ” ተባብሎ የኖረ ነው። ጡት ሳይቀር ተጋርቶ ያደገው ሕጻን ብዙ ነው። በከተሞች ብልጭ ድርግም ባይ መብራቶች የተጋረደ ብዙ ያልታየ ሕዝብ አለ። በአካባቢ መቀየር እንኳን የኑሮ ቀውስ የሚገጥመው ሕዝብ ነው።
 
“ጠላቶችህ ናቸው” ብላችሁ ስለወዳጆቹ ክፉ ለመንገር የምትደክሙለት ሕዝብ ያን ያህልም ክፉና ደግ የማይለይ እንዳልሆነ እንኳን አትገነዘቡም። ንቃችሁት ተነስታችሁ ነው እናስከብርህ የምትሉት። ከዚህ በላይ ‘እየታገልኩልህ ነው’ የሚሉትን አለማወቅ የለም!
 
የወገኖቻችን ደም በከንቱ ፈሶ አይቀርም!
 
ይጮሃል! ሁሌም ይጮኻል! ከጩኸቶቹ ሁሉም የጎላና የከበደ የሚሆነው፥ ‘ምሁራን’ ተሰብስበው ደሙን ሊያቃልሉበትና፣ ለጠላቶቹ መስዋዕት ሊገብሩበት እንደሆነ ያወቀ ጊዜ ሳይሆን አይቀርም።
 
የደፈረሰው ጠርቶ፣ የተከፈለው መስዋዕት እንደሚያጠባብቀንና ልቦቻችንን አክሞ በጋራ እንደሚያኖረን፣ አገሪቱንም ለሰው ልጆች ሁሉ የሚመች ስርዓት የሰፈነባት እንደሚያደርግ አልማለሁ!
 
ከዛሬ ነገ ይሻላል!
 
#Ethiopia

It will not be far…

The internet blackout and blockage of social networks in #Ethiopia is a blessing in disguise; and another big strategic mistake of the brutal government. It is a significant add-on to the mass protests, and tells the World once more again about the kind of government we have. As well, it has a good effect of letting the people focus on the effective and less costly interventions.
 
Our cyber activities were, somehow, keeping us aback from proper understanding of the extent that our freedom of speech is banned, and our potentials to get rid of it. Innermost, ‘being an active user of the internet’ might have created a humdrum feeling, and vapid feelings of ‘freedom fighter’ with every status update made and with every conversation held, while it hasn’t even kept us an inch closer to what is required and to our capacity.
 
If people are forced to logout facebook and other social networks, what the hell the tyrants are expecting them to do? They will login to the real world, and get organised in their communities to the fullest, so as to let brutality logout of the land for once and for all. The brutal regime is working hard to let that materialize, and organizing the people for a good cause of getting freedom.
 
Change is inevitable!, as “change will not come if we wait for some other person or some other time. We are the ones we have been waiting for. We are the change that we seek.” (Barack Obama) …and here we’re awake!, and we’ll stay united!
 
We have also learned that violence is a magic that multiplies defiant souls. When problems become devastating, solutions are promising. Now, the country has concerned and determined citizens more than ever. And speaking up for those who can’t is being a passion and it is being less confused with hard politics, and soon freedom will be a fashion for us to cherish and for our children to live in.
 
I am too positive that fighting for human rights and standing up with morale, in all fields, will be ordinary, not a bravery act for few to practice it and many to get astonished about.
 
It will not be far that they will pay the price; and amid, we will thank them for they are being on the power side of the powerless.

ስለ ሁሉም!

“የማርያም መንገድ ስጠኝ። ዝቅ ብዬ ቁልቁለቱ ላይ ልቁምና ተራራዬን ላብዛው።” ብሎ ጨዋታ ምንም አይጠቅምም። ብሔር ተለይቶ ብቻ የተፈጸመ/የሚፈጸም ነገር ካለ፣ ወይም እንደዚያ የሚወሰውሱ ሰዎች ካሉ እነሱን አወግዛለሁ። አመንነውም ካድነው፣ አገሪቱ ላይ እንደ ሁለተኛ ዜጋ ሲሰማው የኖረ ብዙ ሰው አለ። ሀተታ እና ማስረጃ ሳያስፈልገው፥ ኢህአዴግ ይህን ማድረጉ ይታወቃል። ሀላፊነቱንም ራሱ ይወስዳል።
 
“የትግራይ ህዝብ ከመተማ ተለይቶ ተሰደደ፣ ቤቱ ተቃጠለ፣ ጥቃት ተፈጸመበት።” የተባለው ወሬ እውነት ከሆነ፥ በዋናነት ሀላፊነቱን የሚወስደው ኢህአዴግ ነው። “እውነት ከሆነ” ያልኩት፥ ተቃውሞዎች መሰማት ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ፣ ያለውን ጫና እና የጥቃት ልክ ስንሰማ የኖርንባቸው ሚዲያዎች፥ በዚህ ዙሪያ የዘገቡት ነገር ስለሌለ ነው። አገር ውስጥ ያለ ነጻ ሚዲያም የለምና እንዲህ ያለውን ወሬ የሚዘግብ አናገኝም። ሌላው ቀርቶ፥ “አመጽ ቀስቃሽ መጽሐፍ ይዘህ ዞረሃል” ብሎ መጽሐፍ አዟሪዎችን የማሰር ዜና ከሰማንም ሳምንት አልሆነውም።
 
የመንግስት ሚዲያ እንደው እንደከብት ዓይን አረንጓዴ እንጂ ራሱ የሚቀምመውን ቀይ ቀለም እንኳን አያሳይም። የሌለ ልማት እና ሰላም፣ እንጂ ሌላ ሌላ ነገር ሲወራ እንዳንሰማ ተፈርዶብናል። የተወራ ቀንም ለመግለጫ፣ ለዛቻ፣ ሕዝቡን በአንዳንድ የከተማ ነዋሪዎች ለማስመከር፣ እንዲሁም “ታድለው ምንም አይሰማቸውም” ለማስባል፣ እና ለስም መስጠት ነው። ስለዚህ ኢህአዴግ ሀላፊነቱን የሚወስደው፥ ሚዲያዎችን በማፈን፣ አገር ውስጥ የሚከናወኑ ጉዳዮች በእኩል መጠን የዜና ሽፋን እንዲያገኙ ስለማይፈቅድም ጭምር ነው። በፌስቡክ እንኳን ሰዉ በመረጃ ክፍተቱን ቢሞላ፥ እንዴት ጥርስ እንደነከሱባት በዶክመንተሪ እና በየስብሰባው እያነሱት አሳይተውናል።
 
የፈሰሰውን ደም እና ያለውን ተቃውሞ ከመዘገብ ይልቅ ያልዘራውን ማሳ፥ “አሸተ ጎመራ” ብሎ ማሳየት ነው የሚቀለው። ባለፈው ፈይሳ ሌሊሳ እጁን ቢያጣምር እና ተቃውሞውን ሲያሳይ ቀጥታ ቢታይ፥ መብራቱን ደረገሙት። እንግዲህ የኢህአዴግ ሚዲያ ከዚህ ከፍም ዝቅም የለውም። ስለዚህ ዜናዎች በአግባቡ እንዳይደርሱ እና እኩል ዘገባ እንዳያገኙ ከማድረግ ጀምሮ ለተጫወታቸው መሰሪ ሚናዎች ሁሉ ሀላፊነቱን ይወስዳል።
 
ስለዚህ፥ የትግራይ ሕዝብ ላይ ተለይቶ በሕዝብ ጥቃት ተፈጽሟል ብለው ያመኑ ሰዎች፥ ከሰፊው ሕዝብ ጋር ወግነው፣ መንግስትን የሚያወግዙበት እና “በቃህ” የሚሉበት ትክክለኛ ጊዜ ነው። ቢያንስ እሱን ሲያወግዙ ከስር ከስሩ ግድያውን እና ጅምላ ጨራሽ አዋጁን ማውገዝ ቀላል ነገር ሆኖ ተሰሚነትን ያስተርፋል። በዚያም ላይ፥ የዘረኝነትን ሴራ በመሸረብ ሲወጣ ሲወርድ የነበረውም ኢህአዴግ ስለሆነ እሱን በጋራ ማውገዝ እና አንድ ላይ በመሆን አምባገነንነት እንደማያሸንፍ ማሳወቅ ነው።
 
ተቃውሞ ስለማይረፍድ (መንግስትን መቃወም ማለት ሰፊው ሕዝብን መደገፍ ማለት መሆኑም እየታወቀ)፣ ከተጠቁት ወገን ሆኖ ኢህአዴግን በአደባባይ ስላወጀው ግድያ ማውገዝ ፈጣን መፍትሄ ይሆናል። አንዱ ቢጀምረው ሺ ምንተ ሺው ይከተላል። ሀበሻ ደግሞ በአንድ መፈክር ዞሮ ይገናኛል። Trust me, if it is heartfelt, unity is a slogan away!, and it will only terrify the bloody government.
 
የዘረኝነት ድርጊት ካለ ቋቱ ኢህአዴግ ጉያ ስር ነው። ዋናው ጠላታችን ለራሳችን ያለን ስሜት (ego) ነው። ሌላው ጠላታችን ደግሞ ነገሩን ቆመን የምንመለከትበት ቦታ ነው። ዳገት ላይ ቢቆሙ ቁልቁለት ነው የሚታየው። ቁልቁለት ላይ ቢቆሙ ደግሞ ዳገት ነው የሚታየው። እና አቋቋምን ለማስተካከል በመጣር ቢያንስ ጥፋትን መቀነስ ይቻላል። ጨካኞች ቀጥለው ነው የሚያጠቁን።
 
የትግራይ ሆነ የአማራ፥ የሰው ልጆችን መጎሳቆል ማየት የማይፈልግ ሰው፣ በውስጡ ሰብዓዊነት ይኖራልና፥ “ትግራይ ተለይቶ ጉዳት ደረሰበት” ካለ፥ የሌላውንም ጉዳት እኩል ዘግቦ ማውገዝ አለበት። መሞት እጣ ፈንታ በሆነበት አገር ላይ፥ ወደ ሱዳን መሰደድ እንደ እድል ሲቆጠር ቢታይም ብዙ አያስፈርድም።
 
አምባገነኑን መንግስት በመቃወምና፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ሀማደ የታወጀውን ጅምላ ግድያ ለመቋቋም መከራውን እየበላ ያለ ሁሉም፥ ትግሉ ከስርዓቱ ጋር መሆኑን በማወቅ ጥቃት ያልፈጸመበት ሕዝብ ላይ ምንም እንዳያደርግ ሊጠነቀቅ ይገባል። የአምባገነኑ መንግስት አካላትም ቢሆኑ፥ የድርጅታቸውን እድሜ ለማራዘም ጥቃቱን ከሕዝብ ለሕዝብ የተፈጸመ በማስመሰል አድርገው ሊያደርጉ ይችላሉና እነሱንም ነቅቶ ማየት ያሻል።
 
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

ፈርኦናዊነት

Hailemariam-Desalegnሰው ከመጽሐፍ ቢቀር ከእድሜው፣ ከእድሜው ቢቀር ከወዳጆቹ/ጎረቤቶቹ፣ ከነሱ ቢቀር አለትን ወደ አፈር በሚለውጠው ጊዜ፣ ከእርሱም ቢቀር ጨለማና ብርሃን ከሚፈራረቁበት የጠፈጥሮ ዑደት… እንዴት አይማርም?
 
በእኔ እምነት ይሄ ስርዓት እንኳን አሁንና ድሮም ያልፈረሰ፣ በከባድ ችግር ውስጥ እንኳን ገብቶ የማይፈርስ ስርዓት ነው። ስለዚህ በአለት ላይ የተመሰረተ ስርዓት አለን ብሎ ማመን ጠቃሚ ይሆናል። ….በዚህ ሂደት ውስጥ የተሳተፉ አካላትን ያለምህረት ህግ የማስከበር ስራችንን ማከናወን የሚገባን ይሆናል። መንግስት የህግ የበላይነትን ለማስከበር ሁሉንም አቅሙን ይጠቀማል። በእኔ በኩል ይህ የህግ የበላይነት እንዲከበር ለማድረግ ሁሉም የጸጥታ አካሎቻችን ህግ የበላይነትን እንዲያስከብሩ አዝዣለሁ።
ብሏል (ጠ/ሚ?) ኃይለማርያም ደሳለኝ
እንግዲህ ትዕዛዝ ማንበብ ነበርና ስልጣኑ’አለሁ’ ለማለት ጊዜ ተራው ደርሶት መሆኑ ነው ሕዝብ ለመፍጀት ትዕዛዝ ያስተላለፈው፡፡ ይሄ መቼም የሚረሳ ጉዳይ አይደለም!
 
ቃል በቃል ገልብጬው ደጋግሜ አነበብኩት። ደጋግሜ ነፈርኩኝ። የሰው ልጅ አእምሮ እንዴት በዚህ ደረጃ ሊደነዝዝ ይችላል? መቼስ ያደገ አገር ሰዎች ብንሆን እንዲህ ያለውን ሰው ሰብስበው ጥናት መከናወኑ አይቀርም ነበር።
 
“ፀጉራም ውሻ አለ ሲሉት ይሞታል” ነበር ተረቱ። “ፀጉራም ውሻ ሞቶም ሲታይ ጣረ ሞቱ ‘አለሁ’ ይላል” እንበለው ይሆን?!
.
.
ሰውዬው በሀይማኖተኛ ማሊያም እንደሚጫወት ትዝ ቢለን፥ ከመጽሐፍ ቅዱስ የፈርኦንን ታሪክ እናስታውሳለን….
 
“እግዚአብሔር እንደ ተናገረ፥ የፈርዖን ልብ ጸና፥ አልሰማቸውምም። እግዚአብሔርም ሙሴን አለው፦ የፈርዖን ልብ ደነደነ፥ ሕዝቡንም ለመልቀቅ እንቢ አለ።” (ኦሪት ዘጸአት 7፥ 13-14) “ግብፃውያንም፥ የፈርዖን ፈረሶችና ሰረገሎች ፈረሰኞቹም ሁሉ፥ እያሳደዱ በኋላቸው ወደ ባሕር መካከል ገቡ።” (ኦሪት ዘጸአት 14፥23)
 
“የሰው ልጅ ሆይ፥ ስለ ግብጽ ንጉሥ ስለ ፈርዖን ሙሾ አሙሽ፥ እንዲህም በለው። የአሕዛብን አንበሳ መስለህ ነበር፥ ነገር ግን እንደ ባሕር ዘንዶ ሆነሃል በወንዞችህም ወጥተሃል፥ ወኃውንም በእግርህ አደፍርሰሃል፥ ወንዞችህንም አሳድፈሃል።” (ትንቢተ ሕዝቅኤል 32፥2
 
“የመለስ መንፈስ ከኃይለማርያም ላይ ልቀቅ!” የምንልበት ጊዜ አልፏል። አሁን መንፈሱ ሙሉ ለሙሉ እንደተዋሃደው እያየን ነው። …እንግዲህ ሙሾ እያሞሸን ፍትህ ሲፈጸም የምናይበት ቀን ይመጣል! የሰው ልጅ ደም እንደው በከንቱ ፈሶ አይቀርም!
 
“ፈርዖንንና ሠራዊቱን በኤርትራ ባሕር የጣለ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና!” (መዝሙረ ዳዊት 136፥15)
 

ፈይሳን አትንኩት!

14067671_1461358120547331_7833434000898986507_nI can’t keep the brave #FeyisaLelisa out of my mind, I can’t keep him out of my soul. It needs an altruist soul to forgo comfort zone to help the helpless, and to be voice to the voiceless majority. He could have lived in a selective ignorance, and act as if ‘nothing is wrong in the country’ as many have chosen.
 
In fact, he knew that it may cost him career, friends, families, and even breath; as even simple trial of exercising freedom of speech may cost career, freedom of movement, close friends (that play ‘I hate politics’ and/or ‘I am neutral’), neighbors, and life. But he has loved the people, and choose to submit for his own conscience.
 
It is just one of the simplified and contemporary forms of Walk of Jesus. His courageous selfless act is an ever inspirational deed to a generation in general. This is what ‘living well’ means!, what ‘living to the fullest’ means. ‘Thank You’ is an understatement. May his kinds of souls multiply in all sectors. May God be with him and his loved ones throughout.
አትንኩት!
——
ሚዛን ነው – ለክብር
መስፈሪያ – ለፍቅር፣
ፈዋሽ – ከበሽታ፥
አበባ – ለደስታ፤
ምውት – ለእምነቱ፣
ታዛዥ – ለስሜቱ፤
 
ይልቅ ተንጋግታችሁ፥
ቅሰሙ፣ ተማሩ፣
በእጁ ይዳብሳችሁ፣
ተሰለፉ ከእግሩ፤
 
በየቦታው ይኑር፥
ሁሉም በየግብሩ፣
የተከሉት ይመር፣
ይታከም አገሩ፤
 
ስለሕዝብ ማቃሰት፣
ዓለም ደስታን ትቶ፥
ስለአገር መዋተት፣
ቤት ንብረት ረስቶ፥
 
ማሰማት እሮሮ
ባልጠነከረ ልብ
ባልሰላ አእምሮ፥
አይገኝም ከቶ!
ደርሶ ካላሳየን፥
ድንገት ሰው ተነስቶ!
 
“ሃምሳ ሰው ቢወለድ
ሃምሳ ጉድ ይመጣል”
 
ሃምሳ ጀግና ቢወድቅ
ሃምሳ ሺህ ይነሳል፤
 
ሃምሳ ዘር ቢበተን
ማሳ ሰብሎ ያምራል፤
 
ይኸው በዚህ ጊዜም
በአንዱ ሰው ፈይሳ
ሺ ልሳን ተነሳ፣
 
በደልን ምለሳ፣
ግድያን ወቀሳ፣
አፈናን ፍወሳ፣
ጭቆናን ምየሳ።
 
/ዮሐንስ ሞላ/

ከመንግስት ደጋፊዎች ጋር ያለብኝ ችግር፥

ኢአዴግን ስለሚደግፉ ነው?
አይደለም!
 
በፖለቲካ ዝንባሌያቸው ወይም በገዢው ፓርቲ አባልነታቸው ነው?
አይደለም!
 
ይልቅስ፥
ደጋፊነታቸውን ተጠቅመው ግፍንና በደልን ማውገዝ ቀርቶ፥ እንዳልተፈጸመ ሁሉ ችላ ስለሚሉ ነው!
ሁሉን ነገር በዘረኝነት መነጽር ተመልክተው፥ “ወገኔን የነካ ይነካ” ስለሚሉ ነው!
በአባልነታቸውና የደጋፊነት ጠባያቸው የተነሳ ብቻ ጥቅማ ጥቅሞች ሲደረጉላቸው ተስገብግበው ሆዳቸው ውስጥ ስለሚከቱ ነው!
በፖለቲካ ተሳትፏቸው ተመዝነው በምሁራን ላይ ሳይቀር ህልቅና ሲሰጣቸው ትንሽም ሸምቀቅ ሳይሉ በአምባገነንነት ለመሰልጠን ስለማይፈሩ ነው!
መንግስትን ቅዱስ ስለሚያስመስሉ ነው!
የምንኖረውን የኑሮ ዓይነት አገላለጽ ሊያስተምሩን ስለሚፈልጉ ነው!
አገሪቱ ከእድገትና ልማት ውጭ ምንም ችግር አይወራባትም ስለሚሉ ነው!
የሀሳብ ጥልቀትንና የአነጋገር ብስለትን መጠንከር ስለሚፈሩ ነው!
ለማይረባ ጥቅም ብለው ወዳጆቻቸውን አሳልፈው ስለሚሰጡ ነው!
መንግስትን የቤተሰብ ጉባኤ ስለሚያምታቱትና ተቃዋሚዎችን ሁሉ ጠላት እና ፀረ ሰላም ስለሚያስመስሉ ነው!
ትግሬ ሁሉ ኢህአዴግ፣ ኢህአዴግም የትግሬ ብቻ (mind you, ሕወአት አላልኩም።) እንደሆነ ለማስመሰል ስለሚኳትኑ ነው!
አገሩም የመንግስትና የደጋፊዎቹ ብቻ እንደሆነ ስለሚያምኑና፣ በዛቻ፣ በማስፈራሪያ እና የተለያየ ዓይነት ጥቃት በመፈጸም ሊያሳምኑን ስለሚታገሉ ነው!
በገዛ አገራችን ላይ ሁሉን ነገር እኛ ብቻ እናውቅላችኋለን ስለሚሉ ነው!
ወዘተ!
—–
ሕዝብ እንደው “በቃን!” ካለ ሰንብቷል! ምናለ በከንቱ ከመውተርተርና ሕዝብ ከመፍጀት እነሱም ገገማነቱ እና በውሸት ቅንብር መባዘኑ ‪#‎በቃን‬ ብለው በሰላሙ ቢወያዩና ልባቸውን መልሰው ስህተቶቻቸውን ስለማረም ቢያስቡ? በዘውግ ፌደራሊዝም ስም የዘሩትን እያጨዱ ነው። አሁን “ጆሮ ዳባ ልበስ” ብለው ኖረው፥ በማለቅለቅ ላይ ያሉ ጥቅመኛ ኮካዎች እና ሹመኞች ሁሉ የሰብዓዊ መብት ታጋዮች ሆነው መጥተዋል። ግን ምስኪኑን ሕዝብ በግፍ ማጨዱን ቢያቆሙ ምናለ?
የዘረኝነት አስተሳሰብ ይውደም!
 
#Ethiopia 
I would rather go blind than to see the corpse of the massacred children, mothers, and youth; I would rather go deaf than hearing the groans, the wails, and the sobs here and there; I would rather go palsy than standing helplessly and hopelessly in the middle of nowhere. May the souls of the deceased rest in peace, may the wounds of the injured heal fast, and God comfort the grieving souls 😦
 
May the Almighty intervene in the #OromoProtest, and the vain blood sheds of civilians.
 
“To speak of this is painful for me:
to keep silence is no less pain.
On every side is suffering.”
 
— Aeschylus’ Prometheus Bound (as cited on Tower in the Sky)